የማርቆስ ወንጌል (Mark)
1
1
የእግዚአብሔር
ልጅ
የኢየሱስ
ክርስቶስ
ወንጌል
መጀመሪያ
።
2-3
እነሆ
፥
መንገድህን
የሚጠርግ
መልክተኛዬን
በፊትህ
እልካለሁ
የጌታን
መንገድ
አዘጋጁ
ጥርጊያውንም
አቅኑ
እያለ
በምድረ
በዳ
የሚጮኽ
ሰው
ድምፅ
ተብሎ
በነቢዩ
በኢሳይያስ
እንደ
ተጻፈ
፥
4
ዮሐንስ
በምድረ
በዳ
እያጠመቀ
የንስሐንም
ጥምቀት
ለኃጢአት
ስርየት
እየሰበከ
መጣ
።
5
የይሁዳም
አገር
ሁሉ
የኢየሩሳሌምም
ሰዎች
ሁሉ
ወደ
እርሱ
ይወጡ
ነበር
፥
ኃጢአታቸውንም
እየተናዘዙ
በዮርዳኖስ
ወንዝ
ከእርሱ
ይጠመቁ
ነበር
።
6
ዮሐንስም
የግመል
ጠጉር
ለብሶ
በወገቡ
ጠፍር
ይታጠቅ
አንበጣና
የበረሀ
ማርም
ይበላ
ነበር
።
7
ተጎንብሼ
የጫማውን
ጠፍር
መፍታት
የማይገባኝ
ከእኔ
የሚበረታ
በኋላዬ
ይመጣል
።
8
እኔ
በውኃ
አጠመቅኋችሁ
እርሱ
ግን
በመንፈስ
ቅዱስ
ያጠምቃችኋል
እያለ
ይሰብክ
ነበር
።
9
በዚያ
ወራትም
ኢየሱስ
ከገሊላ
ናዝሬት
መጥቶ
ከዮሐንስ
በዮርዳኖስ
ወንዝ
ተጠመቀ
።
10
ወዲያውም
ከውኃው
በወጣ
ጊዜ
ሰማያት
ሲቀደዱ
መንፈስም
እንደ
ርግብ
ሲወርድበት
አየና
።
የምወድህ
ልጄ
አንተ
ነህ
፥
11
በአንተ
ደስ
ይለኛል
የሚል
ድምፅ
ከሰማያት
መጣ
።
12
ወዲያውም
መንፈስ
ወደ
ምድረ
በዳ
አወጣው
።
13
በምድረ
በዳም
ከሰይጣን
እየተፈተነ
አርባ
ቀን
ሰነበተ
ከአራዊትም
ጋር
ነበረ
፥
መላእክቱም
አገለገሉት
።
14-15
ዮሐንስም
አልፎ
ከተሰጠ
በኋላ
ኢየሱስ
የእግዚአብሔርን
መንግሥት
ወንጌል
እየሰበከና
።
ዘመኑ
ተፈጸመ
የእግዚአብሔርም
መንግሥት
ቀርባለች
ንስሐ
ግቡ
በወንጌልም
እመኑ
እያለ
ወደ
ገሊላ
መጣ
።
16
በገሊላ
ባሕርም
አጠገብ
ሲያልፍ
ስምዖንን
ወንድሙንም
እንድርያስን
መረባቸውን
ወደ
ባሕር
ሲጥሉ
አየ
፥
ዓሣ
አጥማጆች
ነበሩና
።
17
ኢየሱስም
።
በኋላዬ
ኑና
ሰዎችን
አጥማጆች
እንድትሆኑ
አደርጋችኋለሁ
አላቸው
።
18
ወዲያውም
መረባቸውን
ትተው
ተከተሉት
።
19
ከዚያም
ጥቂት
እልፍ
ብሎ
የዘብዴዎስን
ልጅ
ያዕቆብን
ወንድሙንም
ዮሐንስን
ደግሞ
በታንኳ
ላይ
መረባቸውን
ሲያበጁ
አየ
።
20
ወዲያውም
ጠራቸው
አባታቸውንም
ዘብዴዎስን
ከሞያተኞቹ
ጋር
በታንኳ
ላይ
ትተው
ተከትለውት
ሄዱ
።
21
ወደ
ቅፍርናሆምም
ገቡ
፤
ወዲያውም
በሰንበት
ወደ
ምኵራብ
ገብቶ
አስተማረ
።
22
እንደ
ባለ
ሥልጣን
ያስተምራቸው
ነበር
እንጂ
እንደ
ጻፎች
አይደለምና
በትምህርቱ
ተገረሙ
።
23
በዚያን
ጊዜም
በምኩራባቸው
ርኵስ
መንፈስ
ያለው
ሰው
ነበረ
፤
24
እርሱም
።
የናዝሬቱ
ኢየሱስ
ሆይ
፥
ከአንተ
ጋር
ምን
አለን
?
ልታጠፋን
መጣህን
?
ማን
እንደ
ሆንህ
አውቄአለሁ
፥
የእግዚአብሔር
ቅዱሱ
ብሎ
ጮኸ
።
25
ኢየሱስም
።
ዝም
በል
ከእርሱም
ውጣ
ብሎ
ገሠጸው
።
26
ርኵሱም
መንፈስ
አንፈራገጠውና
በታላቅ
ድምፅ
ጮኾ
ከእርሱ
ወጣ
።
27
ሁሉም
።
ይህ
ምንድር
ነው
?
በሥልጣን
ርኵሳን
መናፍስትን
ያዝዛል
፤
እነርሱም
ይታዘዙለታልና
ይህ
አዲስ
ትምህርት
ምንድር
ነው
?
ብለው
እስኪጠያየቁ
ድረስ
አደነቁ
።
28
ዝናውም
ወዲያው
በየስፍራው
ወደ
ገሊላ
ዙሪያ
ሁሉ
ወጣ
።
29
ወዲያውም
ከምኵራብ
ወጥቶ
ከያዕቆብና
ከዮሐንስ
ጋር
ወደ
ስምዖንና
ወደ
እንድርያስ
ቤት
ገባ
።
30
የስምዖንም
አማት
በንዳድ
ታማ
ተኝታ
ነበር
፥
ስለ
እርስዋም
ወዲያው
ነገሩት
።
31
ቀርቦም
እጅዋን
ይዞ
አስነሣት
ንዳዱም
ወዲያው
ለቀቃትና
አገለገለቻቸው
።
32
ፀሐይም
ገብቶ
በመሸ
ጊዜ
፥
የታመሙትንና
አጋንንት
ያደረባቸውን
ሁሉ
ወደ
እርሱ
አመጡ
፤
33
ከተማይቱም
ሁላ
በደጅ
ተሰብስባ
ነበር
።
34
በልዩ
ልዩ
ደዌም
የታመሙትን
ብዙዎችን
ፈወሰ
፥
ብዙዎችንም
አጋንንት
አወጣ
፥
አጋንንትም
ክርስቶስ
መሆኑን
አውቀው
ነበርና
ሊናገሩ
አልፈቀደላቸውም
።
35
ማለዳም
ተነሥቶ
ገና
ሌሊት
ሳለ
ወጣ
ወደ
ምድረ
በዳም
ሄዶ
በዚያ
ጸለየ
።
36
ስምዖንና
ከእርሱ
ጋር
የነበሩትም
ገሥግሠው
ተከተሉት
፥
37
ባገኙትም
ጊዜ
።
ሁሉ
ይፈልጉሃል
አሉት
።
38
እርሱም
።
በዚያ
ደግሞ
ልሰብክ
ወደ
ሌላ
ስፍራ
በቅርብ
ወዳሉ
መንደሮች
እንሂድ
ስለዚህ
ወጥቻለሁና
አላቸው
።
39
በምኵራባቸውም
እየሰበከ
አጋንንትንም
እያወጣ
ወደ
ገሊላ
ሁሉ
መጣ
።
40
ለምጻምም
ወደ
እርሱ
መጥቶ
ተንበረከከና
።
ብትወድስ
ልታነጻኝ
ትችላለህ
ብሎ
ለመነው
።
41
ኢየሱስም
አዘነለት
እጁንም
ዘርግቶ
ዳሰሰውና
።
እወድዳለሁ
፤
ንጻ
አለው
።
42
በተናገረም
ጊዜ
ለምጹ
ወዲያው
ለቀቀውና
ነጻ
።
43
በብርቱም
ተናግሮ
ወዲያው
አወጣው
፤
44
ለማንም
አንዳች
እንዳትናገር
ተጠንቀቅ
፥
ነገር
ግን
ሄደህ
ራስህን
ለካህን
አሳይ
ለእነርሱም
ምስክር
እንዲሆን
ስለ
መንጻትህ
ሙሴ
ያዘዘውን
አቅርብ
አለው
።
45
እርሱ
ግን
ሲወጣ
ብዙ
ሊሰብክና
ነገሩን
ሊያወራ
ጀመረ
፥
ስለዚህም
ኢየሱስ
ተገልጦ
ወደ
ከተማ
መግባት
ወደ
ፊት
ተሳነው
፥
ነገር
ግን
በውጭ
በምድረ
በዳ
ይኖር
ነበር
፤
ከየስፍራውም
ወደ
እርሱ
ይመጡ
ነበር
።
2
1
ከጥቂት
ቀን
በኋላ
ወደ
ቅፍርናሆም
ደግሞ
ገብቶ
በቤት
እንደ
ሆነ
ተሰማ
።
2
በደጅ
ያለው
ስፍራም
እስኪጠባቸው
ድረስ
ብዙ
ሰዎች
ተሰበሰቡ
፤
ቃሉንም
ይነግራቸው
ነበር
።
3
አራት
ሰዎችም
የተሸከሙትን
ሽባ
አመጡለት
።
4
ስለ
ሕዝቡም
ብዛት
ወደ
እርሱ
ማቅረብ
ቢያቅታቸው
እርሱ
ያለበትን
የቤቱን
ጣራ
አነሡ
፥
ነድለውም
ሽባው
የተኛበትን
አልጋ
አወረዱ
።
5
ኢየሱስም
እምነታቸውን
አይቶ
ሽባውን
።
አንተ
ልጅ
፥
ኃጢአትህ
ተሰረየችልህ
አለው
።
6
ከጻፎችም
አንዳንዶቹ
በዚያ
ተቀምጠው
ነበር
በልባቸውም
።
ይህ
ሰው
ስለ
ምን
እንደዚህ
ያለ
ስድብ
ይናገራል
?
7
ከአንዱ
ከእግዚአብሔር
በቀር
ኃጢአት
ሊያስተሰርይ
ማን
ይችላል
?
ብለው
አሰቡ
።
8
ወዲያውም
ኢየሱስ
በልባቸው
እንዲህ
እንዳሰቡ
በመንፈስ
አውቆ
እንዲህ
አላቸው
።
በልባችሁ
ይህን
ስለ
ምን
ታስባላችሁ
?
9
ሽባውን
።
ኃጢአትህ
ተሰረየችልህ
ከማለት
ወይስ
።
ተነሣ
አልጋህንም
ተሸከምና
ሂድ
ከማለት
ማናቸው
ይቀላል
?
10
ነገር
ግን
ለሰው
ልጅ
በምድር
ላይ
ኃጢአትን
ሊያስተሰርይ
ሥልጣን
እንዳለው
እንድታውቁ
፤
11
ሽባውን
።
አንተን
እልሃለሁ
፥
ተነሣ
፥
አልጋህን
ተሸከምና
ወደ
ቤትህ
ሂድ
አለው
።
12
ተነሥቶም
ወዲያው
አልጋውን
ተሸክሞ
በሁሉ
ፊት
ወጣ
፥
ስለዚህም
ሰዎች
ሁሉ
ተገረሙና
።
እንዲህ
ያለ
ከቶ
አላየንም
ብለው
እግዚአብሔርን
አከበሩ
።
13
ደግሞም
በባሕር
አጠገብ
ወጣ
፤
ሕዝቡም
ሁሉ
ወደ
እርሱ
መጡና
አስተማራቸው
።
14
ሲያልፍም
በመቅረጫው
ተቀምጦ
የነበረውን
የእልፍዮስን
ልጅ
ሌዊን
አየና
።
ተከተለኝ
አለው
።
ተነሥቶም
ተከተለው
።
15
በቤቱም
በማዕድ
ተቀምጦ
ሳለ
፥
ብዙ
ቀራጮችና
ኃጢአተኞች
ከኢየሱስና
ከደቀ
መዛሙርቱ
ጋር
ተቀመጡ
፤
ብዙ
ነበሩ
ይከተሉትም
ነበር
።
16
ጻፎችና
ፈሪሳውያንም
ከቀራጮችና
ከኃጢአተኞች
ጋር
ሲበላ
አይተው
ለደቀ
መዛሙርቱ
።
ከቀራ
ጮችና
ከኃጢአተኞች
ጋር
የሚበላና
የሚጠጣ
ስለ
ምንድር
ነው
?
አሉ
።
17
ኢየሱስም
ሰምቶ
።
ሕመምተኞች
እንጂ
ብርቱዎች
ባለ
መድኃኒት
አያስፈልጋቸውም
ኃጢአተኞችን
እንጂ
ጻድቃንን
ልጠራ
አልመጣሁም
አላቸው
።
18
የዮሐንስ
ደቀ
መዛሙርትና
ፈሪሳውያን
ይጦሙ
ነበር
።
መጥተውም
።
የዮሐንስና
የፈሪሳውያን
ደቀ
መዛሙርት
የሚጦሙት
የአንተ
ደቀ
መዛሙርት
ግን
የማይጦሙት
ስለ
ምንድር
ነው
?
አሉት
።
19
ኢየሱስም
አላቸው
።
ሙሽራው
ከእነርሱ
ጋር
ሳለ
ሚዜዎች
ሊጦሙ
ይችላሉን
?
ሙሽራው
ከእነርሱ
ጋር
ሳለ
ሊጦሙ
አይችሉም
።
20
ነገር
ግን
ሙሽራው
ከእነርሱ
የሚወሰድበት
ወራት
ይመጣል
፥
በዚያ
ወራትም
ይጦማሉ
።
21
በአረጀ
ልብስ
አዲስ
እራፊ
የሚጥፍ
የለም
፤
ቢደረግ
ግን
፥
አዲሱ
መጣፊያ
አሮጌውን
ይቦጭቀዋል
፥
መቀደዱም
የባሰ
ይሆናል
።
22
በአረጀ
አቁማዳም
አዲስ
የወይን
ጠጅ
የሚያኖር
የለም
፤
ቢደረግ
ግን
፥
የወይን
ጠጁ
አቁማዳውን
ያፈነዳል
የወይኑም
ጠጅ
ይፈሳል
አቁማዳውም
ይጠፋል
አዲሱን
የወይን
ጠጅ
ግን
በአዲስ
አቁማዳ
ያኖራሉ
።
23
በሰንበትም
በእርሻ
መካከል
ሲያልፍ
ደቀ
መዛሙርቱ
እየሄዱ
እሸት
ይቀጥፉ
ጀመር
።
24
ፈሪሳውያንም
።
እነሆ
፥
በሰንበት
ያልተፈቀደውን
ስለ
ምን
ያደርጋሉ
?
አሉት
።
25
እርሱም
።
ዳዊት
ባስፈለገውና
በተራበ
ጊዜ
፥
እርሱ
አብረውት
ከነበሩት
ጋር
ያደረገውን
፥
አብያተር
ሊቀ
ካህናት
በነበረ
ጊዜ
ወደ
እግዚአብሔር
ቤት
እንደ
ገባ
፥
26
ከካህናት
በቀር
መብላት
ያልተፈቀደውን
የመሥዋዕትን
እንጀራ
እንደ
በላ
፥
ከእርሱም
ጋር
ለነበሩት
እንደ
ሰጣቸው
ከቶ
አላነበባችሁምን
?
አላቸው
።
27
ደግሞ
።
ሰንበት
ስለ
ሰው
ተፈጥሮአል
እንጂ
ሰው
ስለ
ሰንበት
አልተፈጠረም
፤
28
እንዲሁም
የሰው
ልጅ
ለሰንበት
እንኳ
ጌታዋ
ነው
አላቸው
።
3
1
ደግሞም
ወደ
ምኵራብ
ገባ
፥
በዚያም
እጁ
የሰለለች
ሰው
ነበር
፤
2
ሊከሱትም
፥
በሰንበት
ይፈውሰው
እንደ
ሆነ
ይጠባበቁት
ነበር
።
3
እጁ
የሰለለችውንም
ሰው
።
ተነሥተህ
ወደ
መካከል
ና
አለው
።
4
በሰንበት
በጎ
ማድረግ
ተፈቅዶአልን
?
ወይስ
ክፉ
?
ነፍስ
ማዳን
ወይስ
መግደል
?
አላቸው
፤
እነርሱም
ዝም
አሉ
።
5
ስለ
ልባቸውም
ድንዛዜ
አዝኖ
ዙሪያውን
እየተመለከተ
በቍጣ
አያቸው
፥
ሰውየውንም
።
እጅህን
ዘርጋ
አለው
።
6
ዘረጋትም
፥
እጁም
ዳነች
።
ፈሪሳውያንም
ወጥተው
ወዲያው
እንዴት
አድርገው
እንዲያጠፉት
ከሄሮድስ
ወገን
ጋር
ተማከሩበት
።
7
ኢየሱስም
ከደቀ
መዛሙርቱ
ጋር
ወደ
ባህር
ፈቀቅ
አለ
፤
ከገሊላ
የመጡም
ብዙ
ሰዎች
ተከተሉት
፤
8
እንዴት
ትልቅ
ነገርም
እንዳደረገው
ሰምተው
ብዙ
ሰዎች
ከይሁዳ
ከኢየሩሳሌምም
ከኤዶምያስም
ከዮርዳኖስ
ማዶም
ከጢሮስና
ከሲዶና
ምድርም
ወደ
እርሱ
መጡ
።
9
ሰዎቹም
እንዳያጋፉት
ታንኳን
ያቆዩለት
ዘንድ
ደቀ
መዛሙርቱን
አዘዛቸው
፤
10
ብዙ
ሰዎችን
አድኖ
ነበርና
፥
ስለዚህም
ሥቃይ
ያለባቸው
ሁሉ
እንዲዳስሱት
ይወድቁበት
ነበር
።
11
ርኵሳን
መናፍስትም
ባዩት
ጊዜ
በፊቱ
ተደፍተው
።
አንተ
የእግዚአብሔር
ልጅ
ነህ
እያሉ
ጮኹ
።
12
እንዳይገልጡትም
በጣም
አዘዛቸው
።
13
ወደ
ተራራም
ወጣ
፥
ራሱም
የወደዳቸውን
ወደ
እርሱ
ጠራ
፥
ወደ
እርሱም
ሄዱ
።
14
ከእርሱም
ጋር
እንዲኖሩና
ለመስበክ
እንዲልካቸው
፥
15
ድውዮችንም
ሊፈውሱ
አጋንንትንም
ሊያወጡ
ሥልጣን
ይሆንላቸው
ዘንድ
አሥራ
ሁለት
አደረገ
፤
16
ስምዖንንም
ጴጥሮስ
ብሎ
ሰየመው
፤
17
የዘብዴዎስንም
ልጅ
ያዕቆብን
የያዕቆብንም
ወንድም
ዮሐንስን
ቦአኔርጌስ
ብሎ
ሰየማቸው
፥
የነጎድጓድ
ልጆች
ማለት
ነው
፤
18
እንድርያስንም
ፊልጶስንም
በርተሎሜውስንም
ማቴዎስንም
ቶማስንም
የእልፍዮስን
ልጅ
ያዕቆብንም
ታዴዎስንም
ቀነናዊውንም
ስምዖንን
፥
19
አሳልፎ
የሰጠውንም
የአስቆሮቱን
ይሁዳን
።
20
ወደ
ቤትም
መጡ
፤
እንጀራም
መብላት
ስንኳ
እስኪሳናቸው
ድረስ
እንደ
ገና
ብዙ
ሰዎች
ተሰበሰቡ
።
21
ዘመዶቹም
ሰምተው
።
አበደ
ብለዋልና
ሊይዙት
ወጡ
።
22
ከኢየሩሳሌም
የወረዱ
ጻፎችም
።
ብዔል
ዜቡል
አለበት
፤
ደግሞ
።
በአጋንንት
አለቃ
አጋንንትን
ያወጣል
ብለው
ተናገሩ
።
23
እነርሱንም
ወደ
እርሱ
ጠርቶ
በምሳሌ
አላቸው
።
ሰይጣን
ሰይጣንን
ሊያወጣው
እንዴት
ይችላል
?
24
መንግሥትም
እርስ
በርስዋ
ከተለያየች
ያች
መንግሥት
ልትቆም
አትችልም
፤
25
ቤትም
እርስ
በርሱ
ከተለያየ
ያ
ቤት
ሊቆም
አይችልም
።
26
ሰይጣንም
ራሱን
ተቃውሞ
ከተለያየ
፥
መጨረሻ
ይሆንበታል
እንጂ
ሊቆም
አይችልም
።
27
ነገር
ግን
አስቀድሞ
ኃይለኛውን
ሳያስር
ወደ
ኃይለኛው
ቤት
ገብቶ
ዕቃውን
ሊበዘብዝ
የሚችል
የለም
፥
ከዚያም
ወዲያ
ቤቱን
ይበዘብዛል
።
28
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ለሰው
ልጆች
ኃጢአት
ሁሉ
የሚሳደቡትም
ስድብ
ሁሉ
ይሰረይላቸዋል
፤
29
በመንፈስ
ቅዱስ
ላይ
የሚሳደብ
ሁሉ
ግን
የዘላለም
ኃጢአት
ዕዳ
ይሆንበታል
እንጂ
ለዘላለም
አይሰረይለትም
።
30
ርኵስ
መንፈስ
አለበት
ይሉ
ነበርና
።
31
እናቱና
ወንድሞቹም
መጡ
በውጭም
ቆመው
ወደ
እርሱ
ልከው
አስጠሩት
።
32
ብዙ
ሰዎችም
በዙሪያው
ተቀምጠው
ነበሩና
።
እነሆ
፥
እናትህ
ወንድሞችህም
በውጭ
ቆመው
ይፈልጉሃል
አሉት
።
33
መልሶም
።
እናቴ
ማን
ናት
?
ወንድሞቼስ
እነ
ማን
ናቸው
?
አላቸው
።
34
በዙሪያው
ተቀምጠው
ወደ
ነበሩትም
ተመለከተና
።
እነሆ
እናቴ
ወንድሞቼም
።
35
የእግዚአብሔርን
ፈቃድ
የሚያደርግ
ሁሉ
፥
እርሱ
ወንድሜ
ነው
እኅቴም
እናቴም
አለ
።
4
1
ደግሞም
በባሕር
ዳር
ሊያስተምር
ጀመረ
።
እጅግ
ብዙ
ሰዎችም
ወደ
እርሱ
ስለ
ተሰበሰቡ
እርሱ
በታንኳ
ገብቶ
በባሕር
ላይ
ተቀመጠ
፤
ሕዝቡም
ሁሉ
በባሕር
ዳር
በምድር
ላይ
ነበሩ
።
2
በምሳሌም
ብዙ
ያስተምራቸው
ነበር
፥
በትምህርቱም
አላቸው
።
ስሙ
።
3-4
እነሆ
፥
ዘሪ
ሊዘራ
ወጣ
።
ሲዘራም
አንዳንዱ
በመንገድ
ዳር
ወደቀና
ወፎች
መጥተው
በሉት
።
5
ሌላውም
ብዙ
መሬት
በሌለበት
በጭንጫ
ላይ
ወደቀና
ጥልቅ
መሬት
ስላልነበረው
ወዲያው
በቀለ
፤
6
ፀሐይም
ሲወጣ
ጠወለገ
፥
ሥርም
ስላልነበረው
ደረቀ
።
7
ሌላውም
በእሾህ
መካከል
ወደቀ
፥
እሾህም
ወጣና
አነቀው
፥
ፍሬም
አልሰጠም
።
8
ሌላውም
በመልካም
መሬት
ላይ
ወደቀና
ወጥቶ
አድጎ
ፍሬ
ሰጠ
፥
አንዱም
ሠላሳ
አንዱም
ስድሳ
አንዱም
መቶ
አፈራ
።
9
የሚሰማ
ጆሮ
ያለው
ይስማ
አለ
።
10
ብቻውንም
በሆነ
ጊዜ
፥
በዙሪያው
የነበሩት
ከአሥራ
ሁለቱ
ጋር
ስለ
ምሳሌው
ጠየቁት
።
11-12
እንዲህም
አላቸው
።
ለእናንተ
የእግዚአብሔርን
መንግሥት
ምሥጢር
ማወቅ
ተሰጥቶአችኋል
፤
በውጭ
ላሉት
ግን
፥
አይተው
እንዲያዩ
እንዳይመለከቱም
፥
ሰምተውም
እንዲሰሙ
እንዳያስተውሉም
፥
እንዳይመለሱ
ኃጢአታቸውም
እንዳይሰረይላቸው
ነገር
ሁሉ
በምሳሌ
ይሆንባቸዋል
።
13
አላቸውም
።
ይህን
ምሳሌ
አታውቁምን
?
እንዴትስ
ምሳሌዎቹን
ሁሉ
ታውቃላችሁ
?
14
ዘሪው
ቃሉን
ይዘራል
።
ቃልም
በተዘራበት
በመንገድ
ዳር
የሆኑት
እነዚህ
ናቸው
፥
15
በሰሙት
ጊዜም
ሰይጣን
ወዲያው
መጥቶ
በልባቸው
የተዘራውን
ቃል
ይወስዳል
።
16
እንዲሁም
በጭንጫ
ላይ
የተዘሩት
እነዚህ
ናቸው
፥
ቃሉንም
ሰምተው
ወዲያው
በደስታ
ይቀበሉታል
፥
17
ለጊዜውም
ነው
እንጂ
በእነርሱ
ሥር
የላቸውም
፥
ኋላም
በቃሉ
ምክንያት
መከራ
ወይም
ስደት
በሆነ
ጊዜ
ወዲያው
ይሰናከላሉ
።
18
በእሾህም
የተዘሩት
ሌሎች
ናቸው
፥
ቃሉን
የሰሙት
እነዚህ
ናቸው
፥
19
የዚህም
ዓለም
አሳብና
የባለጠግነት
ማታለል
የሌላውም
ነገር
ምኞት
ገብተው
ቃሉን
ያንቃሉ
፥
የማያፈራም
ይሆናል
።
20
በመልካምም
መሬት
የተዘሩት
ቃሉን
ሰምተው
የሚቀበሉት
አንዱም
ሠላሳ
አንዱም
ስድሳ
አንዱም
መቶ
ፍሬ
የሚያፈሩት
እነዚህ
ናቸው
።
21
እንዲህም
አላቸው
።
መብራትን
ከዕንቅብ
ወይስ
ከአልጋ
በታች
ሊያኖሩት
ያመጡታልን
?
በመቅረዝ
ላይ
ሊያኖሩት
አይደለምን
?
22
እንዲገለጥ
ባይሆን
የተሰወረ
የለምና
፤
ወደ
ግልጥ
እንዲመጣ
እንጂ
የተሸሸገ
የለም
።
23
የሚሰማ
ጆሮ
ያለው
ቢኖር
ይስማ
።
24
አላቸውም
።
ምን
እንድትሰሙ
ተጠበቁ
።
በምትሰፍሩበት
መስፈሪያ
ይሰፈርላችኋል
ለእናንተም
ይጨመርላችኋል
።
25
ላለው
ይሰጠዋልና
፤
ከሌለውም
ያው
ያለው
እንኳ
ይወሰድበታል
።
26
እርሱም
አለ
።
በምድር
ዘርን
እንደሚዘራ
ሰው
የእግዚአብሔር
መንግሥት
እንደዚህ
ናት
ሌሊትና
ቀን
ይተኛልም
ይነሣልም
፥
27
እርሱም
እንዴት
እንደሚሆን
ሳያውቅ
ዘሩ
ይበቅላል
ያድግማል
።
28
ምድሪቱም
አውቃ
በመጀመሪያ
ቡቃያ
ኋላም
ዛላ
ኋላም
በዛላው
ፍጹም
ሰብል
ታፈራለች
።
29
ፍሬ
ግን
ሲበስል
መከር
ደርሶአልና
ወዲያው
ማጭድ
ይልካል
።
30
እርሱም
አለ
።
የእግዚአብሔርን
መንግሥት
በምን
እናስመስላታለን
?
ወይስ
በምን
ምሳሌ
እንመስላታለን
?
31
እንደ
ሰናፍጭ
ቅንጣት
ናት
፥
እርስዋም
በምድር
በተዘራች
ጊዜ
በምድር
ካለ
ዘር
ሁሉ
ታንሳለች
፤
በተዘራችም
ጊዜ
ትወጣለች
ከአትክልትም
ሁሉ
የምትበልጥ
ትሆናለች
፥
32
የሰማይ
ወፎችም
በጥላዋ
ሊሰፍሩ
እስኪችሉ
ታላላቅ
ቅርንጫፎች
ታደርጋለች
።
33
መስማትም
በሚችሉበት
መጠን
እነዚህን
በሚመስል
በብዙ
ምሳሌ
ቃሉን
ይነግራቸው
ነበር
፤
ያለ
ምሳሌ
ግን
አልነገራቸውም
፥
34
ለብቻቸውም
ሲሆኑ
ነገሩን
ሁሉ
ለገዛ
ደቀ
መዛሙርቱ
ይፈታላቸው
ነበር
።
35
በዚያም
ቀን
በመሸ
ጊዜ
።
ወደ
ማዶ
እንሻገር
አላቸው
።
36
ሕዝቡንም
ትተው
በታንኳ
እንዲያው
ወሰዱት
፥
ሌሎች
ታንኳዎችም
ከእርሱ
ጋር
ነበሩ
።
37
ብርቱ
ዐውሎ
ነፋስም
ተነሣና
ውኃ
በታንኳይቱ
እስኪሞላ
ድረስ
ማዕበሉ
በታንኳይቱ
ይገባ
ነበር
።
38
እርሱም
በስተኋላዋ
ትራስ
ተንተርሶ
ተኝቶ
ነበር
፤
አንቅተውም
።
መምህር
ሆይ
፥
ስንጠፋ
አይገድህምን
?
አሉት
።
39
ነቅቶም
ነፋሱን
ገሠጸው
ባሕሩንም
።
ዝም
በል
፥
ፀጥ
በል
አለው
።
ነፋሱም
ተወ
ታላቅ
ፀጥታም
ሆነ
።
40
እንዲህ
የምትፈሩ
ስለ
ምን
ነው
?
እንዴትስ
እምነት
የላችሁም
?
አላቸው
።
41
እጅግም
ፈሩና
።
እንግዲህ
ነፋስም
ባሕርም
የሚታዘዙለት
ይህ
ማን
ነው
?
ተባባሉ
።
5
1
ወደ
ባሕር
ማዶም
ወደ
ጌርጌሴኖን
አገር
መጡ
።
2
ከታንኳይቱም
በወጣ
ጊዜ
፥
ርኵስ
መንፈስ
የያዘው
ሰው
ከመቃብር
ወጥቶ
ወዲያው
ተገናኘው
፤
3
እርሱም
በመቃብር
ይኖር
ነበር
፥
በሰንሰለትም
ስንኳ
ማንም
ሊያስረው
በዚያን
ጊዜ
አይችልም
ነበር
፤
4
ብዙ
ጊዜ
በእግር
ብረትና
በሰንሰለት
ይታሰር
ነበርና
ዳሩ
ግን
ሰንሰለቱን
ይበጣጥስ
እግር
ብረቱንም
ይሰባብር
ነበር
፥
ሊያሸንፈውም
የሚችል
አልነበረም
፤
5
ሁልጊዜም
ሌሊትና
ቀን
በመቃብርና
በተራራ
ሆኖ
ይጮኽ
ነበር
ሰውነቱንም
በድንጋይ
ይቧጭር
ነበር
።
6
ኢየሱስንም
ከሩቅ
ባየ
ጊዜ
ሮጦ
ሰገደለት
፥
7
በታላቅ
ድምፅም
እየጮኸ
።
የልዑል
እግዚአብሔር
ልጅ
ኢየሱስ
ሆይ
፥
ከአንተ
ጋር
ምን
አለኝ
?
እንዳታሠቃየኝ
በእግዚአብሔር
አምልሃለሁ
አለ
፤
8
አንተ
ርኵስ
መንፈስ
፥
ከዚህ
ሰው
ውጣ
ብሎት
ነበርና
።
9
ስምህ
ማን
ነው
?
ብሎ
ጠየቀው
።
ብዙዎች
ነንና
ስሜ
ሌጌዎን
ነው
አለው
፥
10
ከአገርም
ውጭ
እንዳይሰዳቸው
አጥብቆ
ለመነው
።
11
በዚያም
በተራራ
ጥግ
ብዙ
የእሪያ
መንጋ
ይሰማራ
ነበርና
።
12
ወደ
እሪያዎቹ
እንድንገባ
ስደደን
ብለው
ለመኑት
።
13
ኢየሱስም
ፈቀደላቸው
።
ርኵሳን
መናፍስቱም
ወጥተው
ወደ
እሪያዎቹ
ገቡ
፥
ሁለት
ሺህም
የሚያህል
መንጋ
ከአፋፉ
ወደ
ባሕር
ተጣደፉና
በባሕር
ሰጠሙ
።
ፍ1
ሌጌዎን
ማለት
ጭፍራ
ማለት
ነው
።
14
እረኞቹም
ሸሽተው
በከተማውና
በአገሩ
አወሩ
፤
ነገሩም
ምን
እንደ
ሆነ
ለማየት
መጡ
።
15
ወደ
ኢየሱስም
መጡ
፥
አጋንንትም
ያደሩበትን
ሌጌዎንም
የነበረበትን
ሰው
ተቀምጦ
ለብሶም
ልቡም
ተመልሶ
አዩና
ፈሩ
።
16
ያዩት
ሰዎችም
አጋንንት
ላደሩበት
ሰው
የሆነውንና
ስለ
እሪያዎቹ
ተረኩላቸው
።
17
ከአገራቸውም
እንዲሄድላቸው
ይለምኑት
ጀመር
።
18
ወደ
ታንኳይቱም
በገባ
ጊዜ
አጋንንት
አድረውበት
የነበረው
ሰው
ከእርሱ
ጋር
እንዲኖር
ለመነው
።
19
ኢየሱስም
አልፈቀደለትም
፥
ነገር
ግን
።
ወደ
ቤትህ
በቤተ
ሰዎችህ
ዘንድ
ሄደህ
ጌታ
እንዴት
ያለ
ታላቅ
ነገር
እንዳደረገልህ
እንዴትስ
እንደ
ማረህ
አውራላቸው
አለው
።
20
ሄዶም
ኢየሱስ
እንዴት
ያለ
ታላቅ
ነገር
እንዳደረገለት
አሥር
ከተማ
በሚባል
አገር
ይሰብክ
ጀመር
፥
ሁሉም
ተደነቁ
።
21
ኢየሱስም
ደግሞ
በታንኳይቱ
ወደ
ማዶ
ከተሻገረ
በኋላ
ብዙ
ሰዎች
ወደ
እርሱ
ተሰበሰቡ
፥
በባሕርም
አጠገብ
ነበረ
።
22
ኢያኢሮስ
የተባለ
ከምኵራብ
አለቆች
አንዱ
መጣ
፤
ባየውም
ጊዜ
በእግሩ
ላይ
ወደቀና
።
23
ታናሽቱ
ልጄ
ልትሞት
ቀርባለችና
እንድትድንና
በሕይወት
እንድትኖር
መጥተህ
እጅህን
ጫንባት
ብሎ
አጥብቆ
ለመነው
።
24
ከእርሱም
ጋር
ሄደ
።
ብዙ
ሕዝብም
ተከተሉት
አጋፉትም
።
25
ከአሥራ
ሁለት
ዓመትም
ጀምሮ
ደም
የሚፈሳት
ሴት
ነበረች
፥
26
ከብዙ
ባለ
መድኃኒቶችም
ብዙ
ተሠቃየች
፤
ገንዘብዋንም
ሁሉ
ከስራ
ባሰባት
እንጂ
ምንም
አልተጠቀመችም
፤
27
የኢየሱስንም
ወሬ
ሰምታ
በስተኋላው
በሰዎች
መካከል
መጥታ
ልብሱን
ዳሰሰች
።
28
ልብሱን
ብቻ
የዳሰስሁ
እንደ
ሆነ
እድናለሁ
ብላለችና
።
29
ወዲያውም
የደምዋ
ምንጭ
ደረቀ
ከሥቃይዋም
እንደዳነች
በሰውነትዋ
አወቀች
።
30
ወዲያውም
ኢየሱስ
ከእርሱ
ኃይል
እንደ
ወጣ
በገዛ
ራሱ
አውቆ
በሕዝቡ
መካከል
ዘወር
ብሎ
።
ልብሴን
የዳሰሰ
ማን
ነው
?
አለ
።
31
ደቀ
መዛሙርቱም
።
ሕዝቡ
ሲያጋፉህ
እያየህ
።
ማን
ዳሰሰኝ
ትላለህን
?
አሉት
።
32
ይህንም
ያደረገችውን
ለማየት
ዘወር
ብሎ
ይመለከት
ነበር
።
33
ሴቲቱ
ግን
የተደረገላትን
ስላወቀች
፥
እየፈራች
እየተንቀጠቀጠችም
፥
መጥታ
በፊቱ
ተደፋች
እውነቱንም
ሁሉ
ነገረችው
።
34
እርሱም
።
ልጄ
ሆይ
፥
እምነትሽ
አድኖሻል
፤
በሰላም
ሂጂ
ከሥቃይሽም
ተፈወሽ
አላት
።
35
እርሱም
ገና
ሲናገር
ከምኵራብ
አለቃው
ቤት
ዘንድ
የመጡት
።
ልጅህ
ሞታለች
፤
ስለ
ምን
መምህሩን
አሁን
ታደክመዋለህ
?
አሉት
።
36
ኢየሱስ
ግን
የተናገሩትን
ቃል
አድምጦ
ለምኵራቡ
አለቃ
።
እመን
ብቻ
እንጂ
አትፍራ
አለው
።
37
ከጴጥሮስም
ከያዕቆብም
ከያዕቆብም
ወንድም
ከዮሐንስ
በቀር
ማንም
እንዲከተለው
አልፈቀደም
።
38
ወደ
ምኵራቡ
አለቃ
ቤትም
መጥቶ
ሰዎች
ሲንጫጩና
ሲያለቅሱ
ዋይታም
ሲያበዙ
አየ
፤
39
ገብቶም
።
ስለ
ምን
ትንጫጫላችሁ
ታለቅሳላችሁም
?
ብላቴናይቱ
ተኝታለች
እንጂ
አልሞተችም
አላቸው
።
40
በጣምም
ሳቁበት
።
እርሱ
ግን
ሁሉን
አስወጥቶ
የብላቴናይቱን
አባትና
እናትም
ከእርሱ
ጋር
የነበሩትንም
ይዞ
ብላቴናይቱ
ወዳለችበት
ገባ
።
41
የብላቴናይቱንም
እጅ
ይዞ
።
ጣሊታ
ቁሚ
አላት
፤
ፍችውም
አንቺ
ብላቴና
ተነሽ
እልሻለሁ
ነው
።
42
ብላቴናይቱም
የአሥራ
ሁለት
ዓመት
ልጅ
ነበረችና
ወዲያው
ቆማ
ተመላለሰች
።
ወዲያውም
ታላቅ
መገረም
ተገረሙ
።
43
ይህንም
ማንም
እንዳያውቅ
አጥብቆ
አዞአቸው
።
የምትበላውን
ስጡአት
አላቸው
።
6
1
ከዚያም
ወጥቶ
ወደ
ገዛ
አገሩ
መጣ
ደቀ
መዛሙርቱም
ተከተሉት
።
2
ሰንበትም
በሆነ
ጊዜ
በምኵራብ
ያስተምር
ጀመር
፤
ብዙዎችም
ሰምተው
ተገረሙና
።
እነዚህን
ነገሮች
ይህ
ከወዴት
አገኛቸው
?
ለዚህ
የተሰጠችው
ጥበብ
ምንድር
ናት
?
በእጁም
የሚደረጉ
እንደነዚህ
ያሉ
ተአምራት
ምንድር
ናቸው
?
3
ይህስ
ጸራቢው
የማርያም
ልጅ
የያቆብም
የዮሳም
የይሁዳም
የስምዖንም
ወንድም
አይደለምን
?
እኅቶቹስ
በዚህ
በእኛ
ዘንድ
አይደሉምን
?
አሉ
፤
ይሰናከሉበትም
ነበር
።
4
ኢየሱስም
።
ነቢይ
ከገዛ
አገሩና
ከገዛ
ዘመዶቹ
ከገዛ
ቤቱም
በቀር
ሳይከበር
አይቀርም
አላቸው
።
5
በዚያም
በጥቂቶች
ድውዮች
ላይ
እጁን
ጭኖ
ከመፈወስ
በቀር
፥
ተአምር
ሊያደርግ
ምንም
አልቻለም
።
6
ስለ
አለማመናቸውም
ተደነቀ
።
በመንደሮችም
እያስተማረ
ይዞር
ነበር
።
7
አስራ
ሁለቱንም
ወደ
እርሱ
ጠራ
ሁለት
ሁለቱንም
ይልካቸው
ጀመር
፥
በርኵሳን
መናፍስትም
ላይ
ሥልጣን
ሰጣቸው
፥
8
ለመንገድም
ከበትር
በቀር
እንጀራም
ቢሆን
ከረጢትም
ቢሆን
መሐለቅም
በመቀነታቸው
ቢሆን
እንዳይዙ
አዘዛቸው
።
9
በእግራችሁ
ጫማ
አድርጉ
እንጂ
ሁለት
እጀ
ጠባብ
አትልበሱ
አለ
።
10
በማናቸውም
ስፍራ
ወደ
ቤት
ብትገቡ
ከዚያ
እስክትወጡ
ድረስ
በዚያው
ተቀመጡ
።
11
ከማይቀበሉአችሁና
ከማይሰሙአችሁ
ስፍራ
ሁሉ
፥
ከዚያ
ወጥታችሁ
ምስክር
ይሆንባቸው
ዘንድ
ከእግራችሁ
በታች
ያለውን
ትቢያ
አራግፉ
።
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ከዚያች
ከተማ
ይልቅ
ለሰዶምና
ለገሞራ
በፍርድ
ቀን
ይቀልላቸዋል
አላቸው
።
12
ወጥተውም
ንስሐ
እንዲገቡ
ሰበኩ
፥
ብዙ
አጋንንትንም
አወጡ
፥
13
ብዙ
ድውዮችንም
ዘይት
እየቀቡ
ፈወሱአቸው
።
14
ስሙም
ተገልጦአልና
ንጉሡ
ሄሮድስ
በሰማ
ጊዜ
።
መጥምቁ
ዮሐንስ
ከሙታን
ተነሥቶአል
ስለዚህም
ኃይል
በእርሱ
ይደረጋል
አለ
።
15
ሌሎችም
።
ኤልያስ
ነው
አሉ
፤
ሌሎችም
።
ከነቢያት
እንደ
አንዱ
ነቢይ
ነው
አሉ
።
16
ሄሮድስ
ግን
ሰምቶ
።
እኔ
ራሱን
ያስቈረጥሁት
ዮሐንስ
ይህ
ነው
እርሱ
ከሙታን
ተነሥቶአል
አለ
።
17
ሄሮድስ
የወንድሙን
የፊልጶስን
ሚስት
ሄሮድያዳን
አግብቶ
ነበርና
በእርስዋ
ምክንያት
ራሱ
ልኮ
ዮሐንስን
አስይዞ
በወኅኒ
አሳስሮት
ነበር
፤
18
ዮሐንስ
ሄሮድስን
።
የወንድምህ
ሚስት
ለአንተ
ልትሆን
አልተፈቀደም
ይለው
ነበርና
።
19
ሄሮድያዳ
ግን
ተቃውማው
ልትገድለው
ትፈልግ
ነበር
አልቻለችም
፤
20
ሄሮድስ
ዮሐንስ
ጻድቅና
ቅዱስ
ሰው
እንደ
ሆነ
አውቆ
ይፈራውና
ይጠባበቀው
ነበር
፤
እርሱንም
ሰምቶ
በብዙ
ነገር
ያመነታ
ነበር
፤
21
በደስታም
ይሰማው
ነበር
።
ሄሮድስም
በተወለደበት
ቀን
ለመኳንንቱና
ለሻለቆቹ
ለገሊላም
ሹማምንት
ግብር
ባደረገ
ጊዜ
ምቹ
ቀን
ሆነላትና
22
የሄሮድያዳ
ልጅ
ገብታ
ስትዘፍን
ሄሮድስንና
ከእርሱ
ጋር
የተቀመጡትን
ደስ
አሰኘቻቸው
።
ንጉሡም
ብላቴናይቱን
።
የምትወጂውን
ሁሉ
ለምኚኝ
እሰጥሽማለሁ
አላት
፤
23
የመንግሥቴ
እኩሌታ
ስንኳ
ቢሆን
የምትለምኚውን
ሁሉ
እሰጥሻለሁ
ብሎ
ማለላት
።
24
ወጥታም
ለእናትዋ
።
ምን
ልለምነው
?
አለች
።
እርስዋም
።
የመጥምቁን
የዮሐንስን
ራስ
አለች
።
25
ወዲያውም
ፈጥና
ወደ
ንጉሡ
ገብታ
።
የመጥምቁን
የዮሐንስን
ራስ
በወጭት
አሁን
ልትሰጠኝ
እወዳለሁ
ብላ
ለመነችው
።
26
ንጉሡም
እጅግ
አዝኖ
ስለ
መሐላው
ከእርሱም
ጋር
ስለ
ተቀመጡት
ሊነሣት
አልወደደም
።
27
ወዲያውም
ንጉሡ
ባለ
ወግ
ልኮ
ራሱን
እንዲያመጣ
አዘዘው
።
ሄዶም
በወኅኒ
ራሱን
ቈረጠ
፥
28
ራሱንም
በወጭት
አምጥቶ
ለብላቴናይቱ
ሰጣት
፥
ብላቴናይቱም
ለእናትዋ
ሰጠች
።
29
ደቀ
መዛሙርቱም
ሰምተው
መጡ
በድኑንም
ወስደው
ቀበሩት
።
30
ሐዋርያትም
ወደ
ኢየሱስ
ተሰብስበው
ያደረጉትንና
ያስተማሩትን
ሁሉ
ነገሩት
።
31
እናንት
ራሳችሁ
ብቻችሁን
ወደ
ምድረ
በዳ
ኑና
ጥቂት
ዕረፉ
አላቸው
፤
የሚመጡና
የሚሄዱ
ብዙዎች
ነበሩና
፥
ለመብላት
እንኳ
ጊዜ
አጡ
።
32
በታንኳውም
ብቻቸውን
ወደ
ምድረ
በዳ
ሄዱ
።
33
ሰዎችም
ሲሄዱ
አዩአቸው
ብዙዎችም
አወቁአቸውና
ከከተሞች
ሁሉ
በእግር
እየሮጡ
ወዲያ
ቀደሙአቸው
ወደ
እርሱም
ተሰበሰቡ
።
34
ኢየሱስም
ወጥቶ
ብዙ
ሕዝብ
አየና
እረኛ
እንደሌላቸው
በጎች
ስለ
ነበሩ
አዘነላቸው
፥
ብዙም
ነገር
ያስተምራቸው
ጀመር
።
35
በዚያን
ጊዜም
ብዙ
ሰዓት
ካለፈ
በኋላ
ደቀ
መዛሙርቱ
ወደ
እርሱ
ቀርበው
።
ቦታው
ምድረ
በዳ
ነው
አሁንም
መሽቶአል
፤
36
የሚበሉት
የላቸውምና
በዙሪያ
ወዳሉ
ገጠሮችና
መንደሮች
ሄደው
እንጀራ
ለራሳቸው
እንዲገዙ
አሰናብታቸው
አሉት
።
37
እርሱ
ግን
መልሶ
።
እናንተ
የሚበሉትን
ስጡአቸው
አላቸው
።
ሄደን
እንጀራ
በሁለት
መቶ
ዲናር
እንግዛላቸውን
?
እንዲበሉም
እንስጣቸውን
?
አሉት
።
38
እርሱም
።
ስንት
እንጀራ
አላችሁ
?
ሂዱና
እዩ
አላቸው
።
ባወቁም
ጊዜ
።
አምስት
፥
ሁለትም
ዓሣ
አሉት
።
39
ሁሉንም
በየክፍሉ
በለመለመ
ሣር
ላይ
እንዲያስቀምጡአቸው
አዘዛቸው
።
40
መቶ
መቶውና
አምሳ
አምሳው
እየሆኑ
በተራ
በተራ
ተቀመጡ
።
41
አምስቱንም
እንጀራ
ሁለቱንም
ዓሣ
ይዞ
ወደ
ሰማይ
አሻቅቦ
አየና
ባረከ
፥
እንጀራውንም
ቈርሶ
እንዲያቀርቡላቸው
ለደቀ
መዛሙርቱ
ሰጠ
፥
42
ሁለቱን
ዓሣ
ደግሞ
ለሁሉ
ከፈለ
።
ሁሉም
በልተው
ጠገቡ
፤
43
ከቍርስራሹም
አሥራ
ሁለት
መሶብ
የሞላ
አነሡ
ከዓሣውም
ደግሞ
።
44
እንጀራውንም
የበሉት
ወንዶቹ
አምስት
ሺህ
ነበሩ
።
45
ወዲያውም
ሕዝቡን
ሲያሰናብት
ሳለ
ደቀ
መዛሙርቱ
በታንኳ
ገብተው
ወደ
ማዶ
ወደ
ቤተ
ሳይዳ
እንዲቀድሙት
ግድ
አላቸው
።
46
ካሰናበታቸውም
በኋላ
ሊጸልይ
ወደ
ተራራ
ወጣ
።
47
በመሸም
ጊዜ
ታንኳይቱ
በባሕር
መካከል
ሳለች
እርሱ
ብቻውን
በምድር
ላይ
ነበረ
።
48
ነፋስ
ወደ
ፊታቸው
ነበረና
እየቀዘፉ
ሲጨነቁ
አይቶ
፥
ከሌሊቱ
በአራተኛው
ክፍል
በባሕር
ላይ
እየሄደ
ወደ
እነርሱ
መጣ
፤
ሊያልፋቸውም
ይወድ
ነበር
።
49
እነርሱ
ግን
በባሕር
ላይ
ሲሄድ
ባዩት
ጊዜ
ምትሀት
መሰላቸውና
ጮኹ
፥
50
ሁሉ
አይተውታልና
፥
ታወኩም
።
ወዲያውም
ተናገራቸውና
።
አይዞአችሁ
፤
እኔ
ነኝ
፥
አትፍሩ
አላቸው
።
51
ወደ
እነርሱም
ወደ
ታንኳይቱ
ገባ
፥
ነፋሱም
ተወ
፤
በራሳቸውም
ያለ
መጠን
እጅግ
ተገረሙ
፤
52
ስለ
እንጀራው
አላስተዋሉምና
፤
ነገር
ግን
ልባቸው
ደንዝዞ
ነበር
።
53
ተሻግረውም
ወደ
ምድር
ወደ
ጌንሴሬጥ
ደረሱ
ታንኳይቱንም
አስጠጉ
።
54
ከታንኳይቱም
ሲወጡ
ወዲያው
አውቀውት
55
በዚያች
አገር
ሁሉ
ዙሪያ
ሮጡና
እርሱ
እንዳለ
ወደ
ሰሙበት
ስፍራ
ሕመምተኞችን
በአልጋ
ላይ
ያመጡ
ጀመር
።
56
በገባበትም
ስፍራ
ሁሉ
፥
መንደርም
ከተማም
ገጠርም
ቢሆን
፥
በገበያ
ድውዮችን
ያኖሩ
ነበር
፤
የልብሱንም
ጫፍ
እንኳ
ሊዳስሱ
ይለምኑት
ነበር
የዳሰሱትም
ሁሉ
ዳኑ
።
7
1
ፈሪሳውያንና
ከጻፎች
ወገን
ከኢየሩሳሌም
የመጡትም
ወደ
እርሱ
ተሰበሰቡ
።
2
ከደቀ
መዛሙርቱም
አንዳንድ
በርኵስ
ማለት
ባልታጠበ
እጅ
እንጀራ
ሲበሉ
አዩ
።
3
ፈሪሳውያንና
አይሁድም
ሁሉ
የሽማግሎችን
ወግ
ሲጠብቁ
እጃቸውን
ደኅና
አድርገው
ሳይታጠቡ
አይበሉምና
፥
4
ከገበያም
ተመልሰው
ካልታጠቡ
አይበሉም
፥
ጽዋንም
ማድጋንም
የናስ
ዕቃንም
አልጋንም
እንደ
ማጠብ
ሌላ
ነገር
ሊጠብቁት
የተቀበሉት
ብዙ
አለ
።
5
ፈሪሳውያንም
ጻፎችም
።
ደቀ
መዛሙርትህ
እንደ
ሽማግሌዎች
ወግ
ስለ
ምን
አይሄዱም
?
ነገር
ግን
እጃቸውን
ሳይታጠቡ
እንጀራ
ይበላሉ
ብለው
ጠየቁት
።
6
እርሱ
ግን
እንዲህ
አላቸው
።
ኢሳይያስ
ስለ
እናንተ
ስለ
ግብዞች
።
ይህ
ሕዝብ
በከንፈሩ
ያከብረኛል
ልቡ
ግን
ከእኔ
በጣም
የራቀ
ነው
፤
7
የሰውም
ሥርዓት
የሆነ
ትምህርት
እያስተማሩ
በከንቱ
ያመልኩኛል
ተብሎ
እንደ
ተጻፈ
በእውነት
ትንቢት
ተናገረ
።
8
የእግዚአብሔርን
ትእዛዝ
ትታችሁ
ጽዋን
ማድጋንም
እንደ
ማጠብ
የሰውን
ወግ
ትጠብቃላችሁ
፥
ይህንም
የመሰለ
ብዙ
ሌላ
ነገር
ታደርጋላችሁ
።
9
እንዲህም
አላቸው
።
ወጋችሁን
ትጠብቁ
ዘንድ
የእግዚአብሔርን
ትእዛዝ
እጅግ
ንቃችኋል
።
10
ሙሴ
።
አባትህንና
እናትህን
አክብር
፤
ደግሞ
።
አባቱን
ወይም
እናቱን
የሰደበ
ፈጽሞ
ይሙት
ብሎአልና
።
11
እናንተ
ግን
ትላላችሁ
።
ሰው
አባቱን
ወይም
እናቱን
።
ከእኔ
የምትጠቀምበት
ነገር
ሁሉ
ቍርባን
ማለት
መባ
ነው
ቢል
፥
12
ለአባቱና
ለእናቱ
ምንም
እንኳ
ሊያደርግ
ወደ
ፊት
አትፈቅዱለትም
፤
13
ባስተላለፋችሁትም
ወግ
የእግዚአብሔርን
ቃል
ትሽራላችሁ
፤
እንደዚሁም
ይህን
የሚመስል
ብዙ
ነገር
ታደርጋላችሁ
።
14
ደግሞም
ሕዝቡን
ጠርቶ
።
ሁላችሁ
እኔን
ስሙ
አስተውሉም
።
15
ከሰው
የሚወጡት
ሰውን
የሚያረክሱ
ናቸው
እንጂ
ከሰው
ውጭ
የሚገባውስ
ሊያረክሰው
የሚችል
ምንም
የለም
።
16
የሚሰማ
ጆሮ
ያለው
ቢኖር
ይስማ
አላቸው
።
17
ከሕዝቡ
ዘንድ
ወደ
ቤት
ከገባ
በኋላ
ደቀ
መዛሙርቱ
ምሳሌውን
ጠየቁት
።
18
እርሱም
።
እናንተ
ደግሞ
እንደዚህ
የማታስተውሉ
ናችሁን
?
ከውጭ
ወደ
ሰው
የሚገባ
ሊያረክሰው
ምንም
እንዳይችል
አትመለከቱምን
?
19
ወደ
ሆድ
ገብቶ
ወደ
እዳሪ
ይወጣል
እንጂ
ወደ
ልብ
አይገባምና
፤
መብልን
ሁሉ
እያጠራ
አላቸው
።
20
እርሱም
አለ
።
ከሰው
የሚወጣው
ሰውን
የሚያረክስ
ያ
ነው
።
21
ከውስጥ
ከሰው
ልብ
የሚወጣ
ክፉ
አሳብ
፥
22
ዝሙት
፥
መስረቅ
፥
መግደል
፥
ምንዝርነት
፥
መጐምጀት
፥
ክፋት
፥
ተንኰል
፥
መዳራት
፥
ምቀኝነት
፥
ስድብ
፥
ትዕቢት
፥
ስንፍና
ናቸውና
፤
23
ይህ
ክፉው
ሁሉ
ከውስጥ
ይወጣል
ሰውን
ያረክሰዋል
።
24
ከዚያም
ተነሥቶ
ወደ
ጢሮስና
ወደ
ሲዶና
አገር
ሄደ
።
ወደ
ቤትም
ገብቶ
ማንም
እንዳያውቅበት
ወደደ
ሊሰወርም
አልተቻለውም
፤
25
ወዲያው
ግን
ታናሺቱ
ልጅዋ
ርኵስ
መንፈስ
ያደረባት
አንዲት
ሴት
ስለ
እርሱ
ሰምታ
መጣችና
በእግሩ
ላይ
ተደፋች
26
ሴቲቱም
ግሪክ
፥
ትውልድዋም
ሲሮፊኒቃዊት
ነበረች
፤
ከልጅዋ
ጋኔን
ያወጣላት
ዘንድ
ለመነችው
።
27
ኢየሱስ
ግን
።
ልጆቹ
በፊት
ይጠግቡ
ዘንድ
ተዪ
የልጆቹን
እንጀራ
ይዞ
ለቡችሎች
መጣል
አይገባምናአላት
።
28
እርስዋም
መልሳ
።
አዎን
፥
ጌታ
ሆይ
፥
ቡችሎች
እንኳ
ከማዕድ
በታች
ሆነው
የልጆችን
ፍርፋሪ
ይበላሉ
አለችው
።
29
እርሱም
።
ስለዚህ
ቃልሽ
ሂጂ
ጋኔኑ
ከልጅሽ
ወጥቶአል
አላት
።
30
ወደ
ቤትዋም
ሄዳ
ጋኔኑ
ወጥቶ
ልጅዋም
በአልጋ
ላይ
ተኝታ
አገኘች
።
31
ደግሞም
ከጢሮስ
አገር
ወጥቶ
በሲዶና
አልፎ
አሥር
ከተማ
በሚባል
አገር
መካከል
ወደ
ገሊላ
ባሕር
መጣ
።
32
ደንቆሮና
ኰልታፋም
የሆነ
ሰው
ወደ
እርሱ
አመጡ
፥
33
እጁንም
ይጭንበት
ዘንድ
ለመኑት
።
ከሕዝቡም
ለይቶ
ለብቻው
ወሰደው
፥
ጣቶቹንም
በጆሮቹ
አገባ
እንትፍም
ብሎ
መላሱን
ዳሰሰ
፤
34
ወደ
ሰማይም
አሻቅቦ
አይቶ
ቃተተና
።
ኤፍታህ
አለው
፥
እርሱም
ተከፈት
ማለት
ነው
።
35
ወዲያውም
ጆሮቹ
ተከፈቱ
የመላሱም
እስራት
ተፈታ
አጥርቶም
ተናገረ
።
36
ለማንም
አትንገሩ
ብሎ
አዘዛቸው
እነርሱ
ግን
ባዘዛቸውም
መጠን
ይልቅ
እጅግ
አወሩት
።
37
ያለ
መጠንም
ተገረሙና
።
ሁሉን
ደኅና
አድርጎአል
፤
ደንቆሮችም
እንዲሰሙ
ዲዳዎችም
እንዲናገሩ
ያደርጋል
አሉ
።
8
1
በዚያ
ወራት
ደግሞ
ብዙ
ሕዝብ
ነበረ
የሚበሉትም
ስለሌላቸው
ደቀ
መዛሙርቱን
ጠርቶ
።
2
ሕዝቡ
ከእኔ
ጋር
እስካሁን
ሦስት
ቀን
ውለዋልና
የሚበሉት
ስለሌላቸው
አዝንላቸዋለሁ
፤
3
ከእነርሱም
አንዳንዶቹ
ከሩቅ
መጥተዋልና
ጦማቸውን
ወደ
ቤታቸው
ባሰናብታቸው
በመንገድ
ይዝላሉ
አላቸው
።
4
ደቀ
መዛሙርቱም
።
በዚህ
በምድረ
በዳ
እንጀራ
ከየት
አግኝቶ
ሰው
እነዚህን
ማጥገብ
ይችላል
?
ብለው
መለሱለት
።
5
እርሱም
።
ስንት
እንጀራ
አላችሁ
?
ብሎ
ጠየቃቸው
፥
እነርሱም
።
ሰባት
አሉት
።
6
ሕዝቡም
በምድር
እንዲቀመጡ
አዘዘ
።
ሰባቱንም
እንጀራ
ይዞ
አመሰገነ
፥
ቈርሶም
እንዲያቀርቡላቸው
ለደቀ
መዛሙርቱ
ሰጠ
፥
ለሕዝቡም
አቀረቡ
።
7
ጥቂትም
ትንሽ
ዓሣ
ነበራቸው
፤
ባረከውም
ይህንም
ደግሞ
እንዲያቀርቡላቸው
አዘዘ
።
8
በሉም
ጠገቡም
፥
የተረፈውንም
ቍርስራሽ
ሰባት
ቅርጫት
አነሡ
።
9
የበሉትም
አራት
ሺህ
ያህል
ነበሩ
።
10
አሰናበታቸውም
።
ወዲያውም
ከደቀ
መዛሙርቱ
ጋር
ወደ
ታንኳይቱ
ገብቶ
ወደ
ዳልማኑታ
አገር
መጣ
።
11
ፈሪሳውያንም
ወጡና
ሊፈትኑት
ከሰማይ
ምልክት
ከእርሱ
ፈልገው
ከእርሱ
ጋር
ይከራከሩ
ጀመር
።
12
በመንፈሱም
እጅግ
ቃተተና
።
ይህ
ትውልድ
ስለ
ምን
ምልክት
ይፈልጋል
?
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ለዚህ
ትውልድ
ምልክት
አይሰጠውም
አለ
።
13
ትቶአቸውም
እንደ
ገና
ወደ
ታንኳይቱ
ገብቶ
ወደ
ማዶ
ሄደ
።
14
እንጀራ
መያዝም
ረሱ
፥
ለእነርሱም
ከአንድ
እንጀራ
በቀር
በታንኳይቱ
አልነበራቸውም
።
15
እርሱም
።
ተጠንቀቁ
፤
ከፈሪሳውያንና
ከሄሮድስ
እርሾ
ተጠበቁ
ብሎ
አዘዛቸው
።
16
እርስ
በርሳቸውም
።
እንጀራ
ስለሌለን
ይሆናል
ብለው
ተነጋገሩ
።
17
ኢየሱስም
አውቆ
እንዲህ
አላቸው
።
እንጀራ
ስለሌላችሁ
ስለ
ምን
ትነጋገራላችሁ
?
ገና
አልተመለከታችሁምን
?
አላስተዋላችሁምን
?
18
ልባችሁስ
ደንዝዞአልን
?
ዓይን
ሳላችሁ
አታዩምን
?
ጆሮስ
ሳላችሁ
አትሰሙምን
?
ትዝስ
አይላችሁምን
?
19
አምስቱን
እንጀራ
ለአምስት
ሺህ
በቈረስሁ
ጊዜ
፥
ቍርስራሹ
የሞላ
ስንት
መሶብ
አነሣችሁ
?
እነርሱም
።
አሥራ
ሁለት
አሉት
።
20
ሰባቱን
እንጀራስ
ለአራት
ሺህ
በቈረስሁ
ጊዜ
፥
ቍርስራሹ
የሞላ
ስንት
ቅርጫት
አነሣችሁ
?
እነርሱም
።
ሰባት
አሉት
።
21
ገና
አላስተዋላችሁምን
?
አላቸው
።
22
ወደ
ቤተ
ሳይዳም
መጡ
።
ዕውርም
አመጡለት
፥
እንዲዳስሰውም
ለመኑት
።
23
ዕውሩንም
እጁን
ይዞ
ከመንደር
ውጭ
አወጣው
፥
በዓይኑም
ተፍቶበት
እጁንም
ጭኖበት
።
አንዳች
ታያለህን
ብሎ
ጠየቀው
።
24
አሻቅቦም
።
ሰዎች
እንደ
ዛፍ
ሲመላለሱ
አያለሁ
አለ
።
25
ከዚህም
በኋላ
ደግሞ
እጁን
በዓይኑ
ላይ
ጫነበት
አጥርቶም
አየና
ዳነም
ከሩቅም
ሳይቀር
ሁሉን
ተመለከተ
።
26
ወደ
ቤቱም
ሰደደውና
።
ወደ
መንደሩ
አትግባ
በመንደሩም
ለማንም
አንዳች
አትናገር
አለው
።
27
ኢየሱስና
ደቀ
መዛሙርቱም
በፊልጶስ
ቂሣርያ
ወዳሉ
መንደሮች
ወጡ
በመንገድም
።
ሰዎች
እኔ
ማን
እንደ
ሆንሁ
ይላሉ
?
ብሎ
ደቀ
መዛሙርቱን
ጠየቃቸው
።
28
እነርሱም
።
መጥምቁ
ዮሐንስ
፥
ሌሎችም
ኤልያስ
፥
ሌሎችም
ከነቢያት
አንዱ
ብለው
ነገሩት
።
29
እናንተስ
እኔ
ማን
እንደ
ሆንሁ
ትላላችሁ
?
ብሎ
ጠየቃቸው
።
ጴጥሮስም
።
አንተ
ክርስቶስ
ነህ
ብሎ
መለሰለት
።
30
ስለ
እርሱም
ለማንም
እንዳይናገሩ
አዘዛቸው
።
31
የሰው
ልጅ
ብዙ
መከራ
ሊቀበል
፥
ከሽማግሌዎችም
ከካህናት
አለቆችም
ከጻፎችም
ሊጣል
፥
ሊገደልም
ከሦስት
ቀንም
በኋላ
ሊነሣ
እንዲገባው
ያስተምራቸው
ጀመር
፤
ቃሉንም
ገልጦ
ይናገር
ነበር
።
32
ጴጥሮስም
ወደ
እርሱ
ወስዶ
ይገሥጸው
ጀመር
።
33
እርሱ
ግን
ዘወር
አለ
ደቀ
መዛሙርቱንም
አይቶ
ጴጥሮስን
ገሠጸውና
።
ወደ
ኋላዬ
ሂድ
፥
አንተ
ሰይጣን
፤
የሰውን
እንጂ
የእግዚአብሔርን
ነገር
አታስብምና
አለው
።
34
ሕዝቡንም
ከደቀ
መዛሙርቱ
ጋር
ጠርቶ
እንዲህ
አላቸው
።
በኋላዬ
ሊመጣ
የሚወድ
ቢኖር
፥
ራሱን
ይካድ
መስቀሉንም
ተሸክሞ
ይከተለኝ
።
35
ነፍሱን
ሊያድን
የሚወድ
ሁሉ
ያጠፋታልና
፥
ስለ
እኔና
ስለ
ወንጌል
ነፍሱን
የሚያጠፋ
ሁሉ
ግን
ያድናታል
።
36
ሰው
ዓለምን
ሁሉ
ቢያተርፍ
ነፍሱንም
ቢያጐድል
ምን
ይጠቅመዋል
?
37
ሰውስ
ስለ
ነፍሱ
ቤዛ
ምን
ይሰጣል
?
38
በዚህም
በዘማዊና
በኃጢአተኛ
ትውልድ
መካከል
በእኔና
በቃሌ
የሚያፍር
ሁሉ
፥
የሰው
ልጅ
ደግሞ
በአባቱ
ክብር
ከቅዱሳን
መላእክት
ጋር
በመጣ
ጊዜ
በእርሱ
ያፍርበታል
።
9
1
እውነት
እላችኋለሁ
፥
በዚህ
ከቆሙት
ሰዎች
የእግዚአብሔር
መንግሥት
በኃይል
ስትመጣ
እስኪያዩ
ድረስ
፥
ሞትን
የማይቀምሱ
አንዳንዶች
አሉ
አላቸው
።
2
ከስድስት
ቀንም
በኋላ
ኢየሱስ
ጴጥሮስንና
ያዕቆብን
ዮሐንስንም
ይዞ
ወደ
ረጅም
ተራራ
ብቻቸውን
አወጣቸው
።
በፊታቸውም
ተለወጠ
፥
ልብሱም
አንጸባረቀ
፤
3
አጣቢም
በምድር
ላይ
እንደዚያ
ሊያነጣው
እስከማይችል
በጣም
ነጭ
ሆነ
።
4
ኤልያስና
ሙሴም
ታዩአቸው
፥
ከኢየሱስም
ጋር
ይነጋገሩ
ነበር
።
5
ጴጥሮስም
መልሶ
ኢየሱስን
።
መምህር
ሆይ
፥
በዚህ
መሆን
ለእኛ
መልካም
ነውና
አንድ
ለአንተ
አንድም
ለሙሴ
አንድም
ለኤልያስ
ሦስት
ዳሶች
እንሥራ
አለው
።
6
እጅግ
ስለ
ፈሩ
የሚለውን
አያውቅም
ነበር
።
7
ደመናም
መጥቶ
ጋረዳቸው
፥
ከደመናውም
።
የምወደው
ልጄ
ይህ
ነው
፥
እርሱን
ስሙት
የሚል
ድምፅ
መጣ
።
8
ድንገትም
ዞረው
ሲመለከቱ
ከእነርሱ
ጋር
ከኢየሱስ
ብቻ
በቀር
ማንንም
አላዩም
።
9
ከተራራውም
ሲወርዱ
የሰው
ልጅ
ከሙታን
እስኪነሣ
ድረስ
ያዩትን
ለማንም
እንዳይነግሩ
አዘዛቸው
።
10
ቃሉንም
ይዘው
።
ከሙታን
መነሣት
ምንድር
ነው
?
እያሉ
እርስ
በርሳቸው
ተጠያየቁ
።
11
እነርሱም
።
ኤልያስ
አስቀድሞ
ሊመጣ
እንዲገባው
ጻፎች
ስለ
ምን
ይላሉ
?
ብለው
ጠየቁት
።
12
እርሱም
መልሶ
።
ኤልያስማ
አስቀድሞ
ይመጣል
ሁሉንም
ያቀናናል
፤
ስለ
ሰው
ልጅም
እንዴት
ተብሎ
ተጽፎአል
?
ብዙ
መከራ
እንዲቀበል
እንዲናቅም
።
13
ነገር
ግን
እላችኋለሁ
፥
ኤልያስ
ደግሞ
መጥቶአል
፥
ስለ
እርሱም
እንደ
ተጸፈ
የወደዱትን
ሁሉ
አደረጉበት
አላቸው
።
14
ወደ
ደቀ
መዛሙርቱም
በመጣ
ጊዜ
ብዙ
ሕዝብ
ሲከብቡአቸው
ጻፎችም
ከእነርሱ
ጋር
ሲከራከሩ
አየ
።
15
ወዲያውም
ሕዝቡ
ሁሉ
ባዩት
ጊዜ
ደነገጡ
፥
ወደ
እርሱም
ሮጠው
እጅ
ነሡት
።
16
ጻፎችንም
።
ስለ
ምን
ከእነርሱ
ጋር
ትከራከራላችሁ
?
ብሎ
ጠየቃቸው
።
17
ከሕዝቡ
አንዱ
መልሶ
።
መምህር
ሆይ
፥
ዲዳ
መንፈስ
ያደረበትን
ልጄን
ወደ
አንተ
አምጥቼአለሁ
፤
18
በያዘውም
ስፍራ
ሁሉ
ይጥለዋል
፤
አረፋም
ይደፍቃል
፥
ጥርሱንም
ያፋጫል
ይደርቃልም
፤
እንዲያወጡለትም
ለደቀ
መዛሙርትህ
ነገርኋቸው
፥
አልቻሉምም
አለው
።
19
እርሱም
መልሶ
።
የማታምን
ትውልድ
ሆይ
፥
እስከመቼ
ከእናንተ
ጋር
እኖራለሁ
?
እስከ
መቼስ
እታገሣችኋለሁ
?
ወደ
እኔ
አምጡት
አላቸው
።
20
ወደ
እርሱም
አመጡት
።
እርሱንም
ባየ
ጊዜ
ያ
መንፈስ
ወዲያው
አንፈራገጠው
፤
ወደ
ምድርም
ወድቆ
አረፋ
እየደፈቀ
ተንፈራፈረ
።
21
አባቱንም
።
ይህ
ከያዘው
ስንት
ዘመን
ነው
?
ብሎ
ጠየቀው
።
እርሱም
።
ከሕፃንነቱ
ጀምሮ
ነው
፤
22
ብዙ
ጊዜም
ሊያጠፋው
ወደ
እሳትም
ወደ
ውኃም
ጣለው
፤
ቢቻልህ
ግን
እዘንልን
እርዳንም
አለው
።
23
ኢየሱስም
።
ቢቻልህ
ትላለህ
፤
ለሚያምን
ሁሉ
ይቻላል
አለው
።
24
ወዲያውም
የብላቴናው
አባት
ጮኾ
።
አምናለሁ
፤
አለማመኔን
እርዳው
አለ
።
25
ኢየሱስም
ሕዝቡ
እንደ
ገና
ሲራወጥ
አይቶ
ርኵሱን
መንፈስ
ገሠጸና
።
አንተ
ዲዳ
ደንቆሮም
መንፈስ
፥
እኔ
አዝሃለሁ
፥
ከእርሱ
ውጣ
እንግዲህም
አትግባበት
አለው
።
26
ጮኾም
እጅግም
አንፈራግጦት
ወጣ
፤
ብዙዎችም
።
ሞተ
እስኪሉ
ድረስ
እንደ
ሙት
ሆነ
።
27
ኢየሱስ
ግን
እጁን
ይዞ
አስነሣው
ቆመም
።
28
ወደ
ቤትም
ከገባ
በኋላ
ደቀ
መዛሙርቱ
።
እኛ
ልናወጣው
ያልቻልን
ስለ
ምንድር
ነው
?
ብለው
ብቻውን
ጠየቁት
።
29
ይህ
ወገን
በጸሎትና
በጦም
ካልሆነ
በምንም
ሊወጣ
አይችልም
አላቸው
።
30-31
ከዚያም
ወጥተው
በገሊላ
በኩል
አለፉ
፤
ደቀ
መዛሙርቱንም
ያስተምር
ስለ
ነበር
ማንም
ያውቅ
ዘንድ
አልወደደም
፤
ለእነርሱም
።
የሰው
ልጅ
በሰዎች
እጅ
አልፎ
ይሰጣል
፥
ይገድሉትማል
፥
ተገድሎም
በሦስተኛው
ቀን
ይነሣል
ይላቸው
ነበር
።
32
እነርሱም
ነገሩን
አላስተዋሉም
፥
እንዳይጠይቁትም
ፈሩ
።
33
ወደ
ቅፍርናሆምም
መጣ
።
በቤትም
ሆኖ
።
በመንገድ
እርስ
በርሳችሁ
ምን
ተነጋገራችሁ
?
ብሎ
ጠየቃቸው
።
34
እነርሱ
ግን
በመንገድ
።
ከሁሉ
የሚበልጥ
ማን
ይሆን
?
ተባብለው
ነበርና
ዝም
አሉ
።
35
ተቀምጦም
አሥራ
ሁለቱን
ጠርቶ
።
ሰው
ፊተኛ
ሊሆን
ቢወድ
ከሁሉ
በኋላ
የሁሉም
አገልጋይ
ይሁን
አላቸው
።
36
ሕፃንም
ይዞ
በመካከላቸው
አቆመው
አቅፎም
።
37
እንደዚህ
ካሉ
ሕፃናት
አንዱን
በስሜ
የሚቀበል
ሁሉ
እኔን
ይቀበላል
፤
የሚቀበለኝም
ሁሉ
የላከኝን
እንጂ
እኔን
አይቀበልም
አላቸው
።
38
ዮሐንስ
መልሶ
።
መምህር
ሆይ
፥
አንድ
ሰው
በስምህ
አጋንንትን
ሲያወጣ
አየነው
፥
39
ስለማይከተለንም
ከለከልነው
አለው
።
ኢየሱስ
ግን
አለ
።
በስሜ
ተአምር
ሠርቶ
በቶሎ
በእኔ
ላይ
ክፉ
መናገር
የሚችል
ማንም
የለምና
አትከልክሉት
፤
40
የማይቃወመን
እርሱ
ከእኛ
ጋር
ነውና
።
41
የክርስቶስ
ስለ
ሆናችሁ
በስሜ
ጽዋ
ውኃ
የሚያጠጣችሁ
ሁሉ
፥
ዋጋው
እንዳይጠፋበት
እውነት
እላችኋለሁ
።
42
በእኔም
ከሚያምኑት
ከእነዚህ
ከታናናሾቹ
አንዱን
የሚያሰናክል
ሁሉ
ትልቅ
የወፍጮ
ድንጋይ
በአንገቱ
ታስሮ
ወደ
ባሕር
ቢጣል
ይሻለው
ነበር
።
43-44
እጅህ
ብታሰናክልህ
ቍረጣት
፤
ሁለት
እጅ
ኖሮህ
ትላቸው
ወደማይሞትበት
እሳቱም
ወደማይጠፋበት
ወደ
ገሃነም
ወደማይጠፋ
እሳት
ከመሄድ
ጕንድሽ
ሆነህ
ወደ
ሕይወት
መግባት
ይሻላል
።
45-46
እግርህ
ብታሰናክልህ
ቍረጣት
፤
ሁለት
እግር
ኖሮህ
ትላቸው
ወደማይሞትበት
እሳቱም
ወደማይጠፋበት
ወደ
ገሃነም
ወደማይጠፋ
እሳት
ከመጣል
አንካሳ
ሆነህ
ወደ
ሕይወት
መግባት
ይሻልሃል
።
47-48
ዓይንህ
ብታሰናክልህ
አውጣት
፤
ሁለት
ዓይን
ኖሮህ
ትላቸው
ወደማይሞትበት
እሳቱም
ወደማይጠፋበት
ወደ
ገሃነመ
እሳት
ከመጣል
አንዲት
ዓይን
ኖራህ
ወደ
እግዚአብሔር
መንግሥት
መግባት
ይሻልሃል
።
49
ሰው
ሁሉ
በእሳት
ይቀመማልና
፥
መሥዋዕትም
ሁሉ
በጨው
ይቀመማል
።
50
ጨው
መልካም
ነው
፤
ጨው
ግን
አልጫ
ቢሆን
በምን
ታጣፍጡታላችሁ
?
በነፍሳችሁ
ጨው
ይኑርባችሁ
፥
እርስ
በርሳችሁም
ተስማሙ
።
10
1
ከዚያም
ተነሥቶ
በዮርዳኖስ
ማዶ
ወደ
ይሁዳ
አገር
መጣ
፥
ደግሞም
ብዙ
ሰዎች
ወደ
እርሱ
ተሰበሰቡ
እንደ
ልማዱም
ደግሞ
ያስተምራቸው
ነበር
።
2
ፈሪሳውያንም
ቀርበው
።
ሰው
ሚስቱን
ሊፈታ
ተፈቅዶለታልን
?
ብለው
ሊፈትኑት
ጠየቁት
።
3
እርሱ
ግን
መልሶ
።
ሙሴ
ምን
አዘዛችሁ
?
አላቸው
።
4
እነርሱም
።
ሙሴስ
የፍችዋን
ጽሕፈት
ጽፎ
እንዲፈታት
ፈቀደ
አሉ
።
5
ኢየሱስም
መልሶ
እንዲህ
አላቸው
።
ስለ
ልባችሁ
ጥንካሬ
ይህችን
ትእዛዝ
ጻፈላችሁ
።
6
ከፍጥረት
መጀመሪያ
ግን
እግዚአብሔር
ወንድና
ሴት
አደረጋቸው
፤
7
ስለዚህ
ሰው
አባቱንና
እናቱን
ይተዋል
ከሚስቱም
ጋር
ይተባበራል
፥
8
ሁለቱም
አንድ
ሥጋ
ይሆናሉ
፤
ስለዚህ
አንድ
ሥጋ
ናቸው
እንጂ
ወደ
ፊት
ሁለት
አይደሉም
።
9
እግዚአብሔር
ያጣመረውን
እንግዲህ
ሰው
አይለየው
።
10
በቤትም
ደግሞ
ደቀ
መዛሙርቱ
ስለዚህ
ነገር
ጠየቁት
።
11
እርሱም
።
ሚስቱን
ፈትቶ
ሌላ
የሚያገባ
ሁሉ
በእርስዋ
ላይ
ያመነዝራል
፤
12
እርስዋም
ባልዋን
ፈትታ
ሌላ
ብታገባ
ታመነዝራለች
አላቸው
።
13
እንዲዳስሳቸውም
ሕፃናትን
ወደ
እርሱ
አመጡ
፤
ደቀ
መዛሙርቱም
ያመጡአቸውን
ገሠጹአቸው
።
14
ኢየሱስ
ግን
አይቶ
ተቈጣና
።
ሕፃናትን
ወደ
እኔ
ይመጡ
ዘንድ
ተዉ
አትከልክሉአቸው
፤
የእግዚአብሔር
መንግሥት
እንደነዚህ
ላሉት
ናትና
።
15
እውነት
እላችኋለሁ
፤
የእግዚአብሔርን
መንግሥት
እንደ
ሕፃን
የማይቀበላት
ሁሉ
ከቶ
አይገባባትም
አላቸው
።
16
አቀፋቸውም
እጁንም
ጭኖ
ባረካቸው
።
17
እርሱም
በመንገድ
ሲወጣ
አንድ
ሰው
ወደ
እርሱ
ሮጦ
ተንበረከከለትና
።
ቸር
መምህር
ሆይ
፥
የዘላለም
ሕይወትን
እወርስ
ዘንድ
ምን
ላድርግ
?
ብሎ
ጠየቀው
።
18
ኢየሱስም
።
ስለ
ምን
ቸር
ትለኛለህ
?
ከአንዱ
ከእግዚአብሔር
በቀር
ቸር
ማንም
የለም
።
19
ትእዛዛትን
ታውቃለህ
፤
አታመንዝር
፥
አትግደል
፥
አትስረቅ
፥
በሐሰት
አትመስክር
፥
አታታልል
፥
አባትህንና
እናትህን
አክብር
አለው
።
20
እርሱም
መልሶ
።
መምህር
ሆይ
፥
ይህን
ሁሉ
ከሕፃንነቴ
ጀምሬ
ጠብቄአለሁ
አለው
።
21
ኢየሱስም
ወደ
እርሱ
ተመልክቶ
ወደደውና
።
አንድ
ነገር
ጐደለህ
፤
ሂድ
፥
ያለህን
ሁሉ
ሽጠህ
ለድሆች
ስጥ
፥
በሰማይም
መዝገብ
ታገኛለህ
፥
መስቀሉንም
ተሸክመህ
ና
፥
ተከተለኝ
አለው
።
22
ነገር
ግን
ስለዚህ
ነገር
ፊቱ
ጠቈረ
፥
ብዙ
ንብረት
ነበረውና
እያዘነም
ሄደ
።
23
ኢየሱስም
ዘወር
ብሎ
አይቶ
ደቀ
መዛሙርቱን
።
ገንዘብ
ላላቸው
ወደ
እግዚአብሔር
መንግሥት
መግባት
እንዴት
ጭንቅ
ይሆናል
አላቸው
።
24
ደቀ
መዛሙርቱም
እነዚህን
ቃሎች
አደነቁ
።
ኢየሱስም
ደግሞ
መልሶ
።
ልጆች
ሆይ
፥
በገንዘብ
ለሚታመኑ
ወደ
እግዚአብሔር
መንግሥት
መግባት
እንዴት
ጭንቅ
ነው
።
25
ባለ
ጠጋ
ወደ
እግዚአብሔር
መንግሥት
ከሚገባ
ግመል
በመርፌ
ቀዳዳ
ቢያልፍ
ይቀላል
አላቸው
።
26
እነርሱም
ያለ
መጠን
ተገረሙና
እርስ
በርሳቸው
።
እንግዲያ
ማን
ሊድን
ይችላል
?
ተባባሉ
።
27
ኢየሱስም
ተመለከታቸውና
።
ይህ
በእግዚአብሔር
ዘንድ
እንጂ
በሰው
ዘንድ
አይቻልም
፤
በእግዚአብሔር
ዘንድ
ሁሉ
ይቻላልና
አለ
።
28
ጴጥሮስም
።
እነሆ
፥
እኛ
ሁሉን
ትተን
ተከተልንህ
ይለው
ጀመር
።
29
ኢየሱስም
መልሶ
እንዲህ
አለ
።
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ስለ
እኔና
ስለ
ወንጌል
ቤትን
ወይም
ወንድሞችን
ወይም
እኅቶችን
ወይም
አባትን
ወይም
እናትን
ወይም
ሚስትን
ወይም
ልጆችን
ወይም
እርሻን
የተወ
፥
30
አሁን
በዚህ
ዘመን
ከስደት
ጋር
ቤቶችን
ወንድሞችንና
እኅቶችንም
እናቶችንም
ልጆችንም
እርሻንም
መቶ
እጥፍ
፥
በሚመጣውም
ዓለም
የዘላለም
ሕይወት
የማይቀበል
ማንም
የለም
።
31
ግን
ብዙ
ፊተኞች
ኋለኞች
ኋለኞችም
ፊተኞች
ይሆናሉ
።
32
ወደ
ኢየሩሳሌምም
ሊወጡ
በመንገድ
ነበሩ
፥
ኢየሱስም
ይቀድማቸው
ነበርና
ተደነቁ
፤
የተከተሉትም
ይፈሩ
ነበር
።
ደግሞም
አሥራ
ሁለቱን
ወደ
እርሱ
አቅርቦ
ይደርስበት
ዘንድ
ያለውን
ይነግራቸው
ጀመር
።
33
እነሆ
፥
ወደ
ኢየሩሳሌም
እንወጣለን
፥
የሰው
ልጅም
ለካህናት
አለቆችና
ለጻፎች
አልፎ
ይሰጣል
፥
የሞት
ፍርድም
ይፈርዱበታል
፥
ለአሕዛብም
አሳልፈው
ይሰጡታል
፥
34
ይዘብቱበትማል
ይተፉበትማል
ይገርፉትማል
ይገድሉትማል
፥
በሦስተኛውም
ቀን
ይነሣል
አላቸው
።
35
የዘብዴዎስ
ልጆች
ያዕቆብና
ዮሐንስም
ወደ
እርሱ
ቀርበው
።
መምህር
ሆይ
፥
የምንለምንህን
ሁሉ
እንድታደርግልን
እንወዳለን
አሉት
።
36
እርሱም
።
ምን
ላደርግላችሁ
ትወዳላችሁ
?
አላቸው
።
37
እነርሱም
።
በክብርህ
ጊዜ
አንዳችን
በቀኝ
አንዳችንም
በግራህ
መቀመጥን
ስጠን
አሉት
።
38
ኢየሱስ
ግን
።
የምትለምኑትን
አታውቁም
።
እኔ
የምጠጣውን
ጽዋ
ልትጠጡ
፥
እኔ
የምጠመቀውንስ
ጥምቀት
ልትጠመቁ
ትችላላችሁን
?
አላቸው
።
39
እነርሱም
።
እንችላለን
አሉት
።
ኢየሱስም
።
እኔ
የምጠጣውን
ጽዋ
ትጠጣላችሁ
፥
እኔ
የምጠመቀውንም
ጥምቀት
ትጠመቃላችሁ
፤
40
በቀኝና
በግራ
መቀመጥ
ግን
ለተዘጋጀላቸው
ነው
እንጂ
የምሰጥ
እኔ
አይደለሁም
አላቸው
።
41
አሥሩም
ሰምተው
በያዕቆብና
በዮሐንስ
ይቈጡ
ጀመር
።
42
ኢየሱስም
ወደ
እርሱ
ጠርቶ
እንዲህ
አላቸው
።
የአሕዛብ
አለቆች
ተብሎ
የምታስቡት
እንዲገዙአቸው
ታላላቆቻቸውም
በላያቸው
እንዲሠለጥኑ
ታውቃላችሁ
።
43
በእናንተስ
እንዲህ
አይደለም
፤
ነገር
ግን
ማንም
ከእናንተ
ታላቅ
ሊሆን
የሚወድ
የእናንተ
አገልጋይ
ይሁን
፥
44
ከእናንተም
ማንም
ፊተኛ
ሊሆን
የሚወድ
የሁሉ
ባሪያ
ይሁን
፤
45
እንዲሁ
የሰው
ልጅም
ሊያገለግልና
ነፍሱን
ለብዙዎች
ቤዛ
ሊሰጥ
እንጂ
እንዲያገለግሉት
አልመጣም
።
46
ወደ
ኢያሪኮም
መጡ
።
ከደቀ
መዛሙርቱና
ከብዙ
ሕዝብ
ጋር
ከኢያሪኮ
ሲወጣ
የጤሜዎስ
ልጅ
ዕውሩ
በርጤሜዎስ
እየለመነ
በመንገድ
ዳር
ተቀምጦ
ነበር
።
47
የናዝሬቱ
ኢየሱስም
እንደ
ሆነ
በሰማ
ጊዜ
።
የዳዊት
ልጅ
ኢየሱስ
ሆይ
፥
ማረኝ
እያለ
ይጮኽ
ጀመር
።
48
ብዙዎችም
ዝም
እንዲል
ገሠጹት
፤
እርሱ
ግን
።
የዳዊት
ልጅ
ሆይ
፥
ማረኝ
እያለ
አብዝቶ
ጮኸ
።
49
ኢየሱስም
ቆመና
።
ጥሩት
አለ
።
ዕውሩንም
።
አይዞህ
፥
ተነሣ
፥
ይጠራሃል
ብለው
ጠሩት
።
50
እርሱም
እየዘለለ
ተነሣና
ልብሱን
ጥሎ
ወደ
ኢየሱስ
መጣ
።
51
ኢየሱስም
መልሶ
።
ምን
ላደርግልህ
ትወዳለህ
?
አለው
።
ዕውሩም
።
መምህር
ሆይ
፥
አይ
ዘንድ
አለው
።
52
ኢየሱስም
።
ሂድ
፤
እምነትህ
አድኖሃል
አለው
።
ወዲያውም
አየ
በመንገድም
ተከተለው
።
11
1
ወደ
ኢየሩሳሌምም
ከደብረ
ዘይት
አጠገብ
ወዳሉቱ
ወደ
ቤተ
ፋጌና
ወደ
ቢታንያ
በቀረቡ
ጊዜ
፥
ከደቀ
መዛሙርቱ
ሁለቱን
ልኮ
።
2
በፊታችሁ
ወዳለችው
መንደር
ሂዱ
፥
ወዲያውም
ወደ
እርስዋ
ገብታችሁ
ከሰው
ማንም
ገና
ያልተቀመጠበት
ውርንጫ
ታስሮ
ታገኛላችሁ
፤
ፈትታችሁ
አምጡልኝ
።
3
ማንም
።
ስለ
ምን
እንዲህ
ታደርጋላችሁ
?
ቢላችሁ
።
ለጌታ
ያስፈልገዋል
በሉት
፥
ወዲያውም
ደግሞ
ወደዚህ
ይሰደዋል
አላቸው
።
4
ሄዱም
ውርንጫውንም
በመንገድ
መተላለፊያ
በደጅ
ውጭ
ታስሮ
አገኙት
፥
ፈቱትም
።
5
በዚያም
ከቆሙት
አንዳንዶቹ
።
ውርንጫውን
የምትፈቱት
ምን
ልታደርጉት
ነው
አሉአቸው
።
6
እነርሱም
ኢየሱስ
እንዳዘዘ
አሉአቸው
፤
ተዉአቸውም
።
7
ውርንጫውንም
ወደ
ኢየሱስ
አመጡት
፥
ልብሳቸውንም
በላዩ
ጣሉ
፥
ተቀመጠበትም
።
8
ብዙ
ሰዎችም
ልብሳቸውን
በመንገድ
ላይ
አነጠፉ
፥
ሌሎችም
ከዛፍ
ቅጠሎችን
እየቈረጡ
ያነጥፉ
ነበር
።
9
የሚቀድሙትም
የሚከተሉትም
።
ሆሣዕና
፤
በጌታ
ስም
የሚመጣ
የተባረከ
ነው
፤
10
በጌታ
ስም
የምትመጣ
የአባታችን
የዳዊት
መንግሥት
የተባረከች
ናት
፤
ሆሣዕና
በአርያም
እያሉ
ይጮኹ
ነበር
።
11
ኢየሱስም
ወደ
ኢየሩሳሌም
ወደ
መቅደስ
ገባ
፤
ዘወር
ብሎም
ሁሉን
ከተመለከተ
በኋላ
፥
ጊዜው
መሽቶ
ስለ
ነበረ
ከአሥራ
ሁለቱ
ጋር
ወደ
ቢታንያ
ወጣ
።
12
በማግሥቱም
ከቢታንያ
ሲወጡ
ተራበ
።
13
ቅጠልም
ያላት
በለስ
ከሩቅ
አይቶ
ምናልባት
አንዳች
ይገኝባት
እንደ
ሆነ
ብሎ
መጣ
፥
ነገር
ግን
የበለስ
ወራት
አልነበረምና
መጥቶ
ከቅጠል
በቀር
ምንም
አላገኘባትም
።
14
መልሶም
።
ከአሁን
ጀምሮ
ለዘላለም
ማንም
ከአንቺ
ፍሬ
አይብላ
አላት
።
ደቀ
መዛሙርቱም
ሰሙ
።
15
ወደ
ኢየሩሳሌምም
መጡ
።
ወደ
መቅደስም
ገብቶ
በመቅደስ
የሚሸጡትንና
የሚገዙትን
ያወጣ
ጀመር
፥
የገንዘብ
ለዋጮችንም
ገበታዎች
የርግብ
ሻጭዎችንም
ወንበሮች
ገለበጠ
፤
16
ዕቃም
ተሸክሞ
ማንም
በመቅደስ
ሊያልፍ
አልፈቀደም
።
17
አስተማራቸውም
።
ቤቴ
ለአሕዛብ
ሁሉ
የጸሎት
ቤት
ትባላለች
ተብሎ
የተጻፈ
አይደለምን
?
እናንተ
ግን
የወንበዶች
ዋሻ
አደረጋችኋት
አላቸው
።
18
የካህናት
አለቆችም
ጻፎችም
ሰምተው
፥
ሕዝቡ
ሁሉ
በትምህርቱ
ይገረሙ
ስለ
ነበር
ይፈሩት
ነበርና
እንዴት
አድርገው
እንዲያጠፉት
ፈለጉ
።
19
ማታ
ማታም
ከከተማ
ወደ
ውጭ
ይወጣ
ነበር
።
20
ማለዳም
ሲያልፉ
በለሲቱን
ከሥርዋ
ደርቃ
አዩአት
።
21
ጴጥሮስም
ትዝ
ብሎት
።
መምህር
ሆይ
፥
እነሆ
፥
የረገምሃት
በለስ
ደርቃለች
አለው
።
22
ኢየሱስም
መልሶ
እንዲህ
አላቸው
።
በእግዚአብሔር
እመኑ
።
23
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ማንም
ያለው
ነገር
እንዲደረግለት
ቢያምን
በልቡ
ሳይጠራጠር
፥
ይህን
ተራራ
።
ተነቅለህ
ወደ
ባሕር
ተወርወር
ቢል
ይሆንለታል
።
24
ስለዚህ
እላችኋለሁ
፥
የጸለያችሁትን
የለመናችሁትንም
ሁሉ
እንዳገኛችሁት
እመኑ
፥
ይሆንላችሁማል
።
25
ለጸሎትም
በቆማችሁ
ጊዜ
፥
በሰማያት
ያለው
አባታችሁ
ደግሞ
ኃጢአታችሁን
ይቅር
እንዲላችሁ
፥
በማንም
ላይ
አንዳች
ቢኖርባችሁ
ይቅር
በሉት
።
26
እናንተ
ግን
ይቅር
ባትሉ
በሰማያት
ያለው
አባታችሁም
ኃጢአታችሁን
ይቅር
አይላችሁም
።
27
ደግሞም
ወደ
ኢየሩሳሌም
መጡ
።
እርሱም
በመቅደስ
ሲመላለስ
፥
የካህናት
አለቆችና
ጻፎች
ሽማግሌዎችም
ወደ
እርሱ
መጥተው
።
28
እነዚህን
በምን
ሥልጣን
ታደርጋለህ
?
ወይስ
እነዚህን
ለማድረግ
ይህን
ሥልጣን
ማን
ሰጠህ
?
አሉት
።
29
ኢየሱስም
።
እኔም
አንዲት
ነገር
እጠይቃችኋለሁ
፥
እናንተም
መልሱልኝ
፥
እኔም
በምን
ሥልጣን
እነዚህን
እንዳደርግ
እነግራችኋለሁ
።
30
የዮሐንስ
ጥምቀት
ከሰማይ
ነበረችን
ወይስ
ከሰው
?
መልሱልኝ
አላቸው
።
31
እርስ
በርሳቸውም
ሲነጋገሩ
።
ከሰማይ
ነው
ብንል
።
እንግዲያውስ
ስለ
ምን
አላመናችሁበትም
?
ይለናል
፤
32
ነገር
ግን
።
ከሰው
ነው
እንበልን
?
አሉ
፤
ሁሉ
ዮሐንስን
በእውነት
እንደ
ነቢይ
ያዩት
ነበርና
ሕዝቡን
ፈሩ
።
33
ለኢየሱስም
መልሰው
።
አናውቅም
አሉት
ኢየሱስም
።
እኔም
በምን
ሥልጣን
እነዚህን
እንዳደርግ
አልነግራችሁም
አላቸው
።
12
1
በምሳሌም
ይነግራቸው
ጀመር
።
አንድ
ሰው
የወይን
አትክልት
ተከለ
፥
ቅጥርም
ቀጠረለት
፥
መጥመቂያም
ማሰለት
፥
ግንብም
ሠራና
ለገበሬዎች
አከራይቶ
ወደ
ሌላ
አገር
ሄደ
።
2
በጊዜውም
ከወይን
አትክልት
ፍሬ
ከገበሬዎቹ
እንዲቀበል
አንድ
ባሪያ
ወደ
ገበሬዎቹ
ላከ
፤
3
ይዘውም
ደበደቡት
ባዶውንም
ሰደዱት
።
4
ዳግመኛም
ሌላውን
ባሪያ
ወደ
እነርሱ
ላከ
እርሱንም
ወግረው
ራሱን
አቈሰሉት
አዋርደውም
ሰደዱት
።
5
ሌላውንም
ላከ
፤
እርሱንም
ገደሉት
፥
ከሌሎችም
ከብዙዎች
አንዳንዱን
ደበደቡ
አንዳንዱንም
ገደሉ
።
6
የሚወደው
አንድ
ልጅ
ገና
ነበረው
፤
ልጄንስ
ያፍሩታል
ብሎ
እርሱን
ከሁሉ
በኋላ
ወደ
እነርሱ
ላከ
።
7
እነዚያ
ገበሬዎች
ግን
እርስ
በርሳቸው
።
ወራሹ
ይህ
ነው
፤
ኑ
፥
እንግደለው
፥
ርስቱም
ለኛ
ይሆናል
ተባባሉ
።
8
ይዘውም
ገደሉት
፥
ከወይኑም
አትክልት
ወደ
ውጭ
ጣሉት
።
9
እንግዲህ
የወይኑ
አትክልት
ጌታ
ምን
ያደርጋል
?
ይመጣል
ገበሬዎቹንም
ያጠፋል
፥
የወይኑንም
አትክልት
ለሌሎች
ይሰጣል
።
10-11
ግንበኞች
የናቁት
ድንጋይ
እርሱ
የማዕዘን
ራስ
ሆነ
፤
ይህም
ከጌታ
ዘንድ
ሆነ
፥
ለዓይኖቻችንም
ድንቅ
ነው
።
የሚለውን
ይህን
መጽሐፍ
አላነበባችሁምን
?
12
ምሳሌውንም
ስለ
እነርሱ
እንደ
ተናገረ
አውቀዋልና
ሊይዙት
ፈለጉ
፥
ነገር
ግን
ሕዝቡን
ፈሩ
።
ትተውትም
ሄዱ
።
13
በንግግርም
ሊያጠምዱት
ከፈሪሳውያንና
ከሄሮድስ
ወገን
የሆኑትን
ወደ
እርሱ
ላኩ
።
14
መጥተውም
።
መምህር
ሆይ
፥
የሰውን
ፊት
ሳትመለከት
በእውነት
የእግዚአብሔር
መንገድ
ታስተምራለህና
እውነተኛ
እንደ
ሆንህ
ለማንምም
እንዳታደላ
እናውቃለን
፤
ለቄሣር
ግብር
መስጠት
ተፈቅዶአልን
ወይስ
አልተፈቀደም
?
እንስጥን
ወይስ
አንስጥ
?
አሉት
።
15
እርሱ
ግን
ግብዝነታቸውን
አውቆ
።
ለምን
ትፈትኑኛላችሁ
?
አየው
ዘንድ
አንድ
ዲናር
አምጡልኝ
አላቸው
።
16
እነርሱም
አመጡለት
።
ይህች
መልክ
ጽሕፈቲቱስ
የማን
ናት
?
አላቸው
፤
እነርሱም
።
የቄሣር
ናት
አሉት
።
17
ኢየሱስም
መልሶ
።
የቄሣርን
ለቄሣር
የእግዚአብሔርንም
ለእግዚአብሔር
አስረክቡ
አላቸው
።
በእርሱም
ተደነቁ
።
18
ትንሣኤ
ሙታን
የለም
የሚሉ
ሰዱቃውያን
ወደ
እርሱ
መጥተው
ጠየቁት
እንዲህም
አሉት
።
19
መምህር
ሆይ
፥
ሙሴ
።
የአንድ
ሰው
ወንድም
ሚስቱን
ትቶ
ልጅ
ሳያስቀር
ቢሞት
፥
ወንድሙ
ሚስቱን
አግብቶ
ለወንድሙ
ዘር
ይተካ
ብሎ
ጻፈልን
።
20
ሰባት
ወንድማማቾች
ነበሩ
፤
ፊተኛውም
ሚስት
አግብቶ
ዘር
ሳያስቀር
ሞተ
፤
21
ሁለተኛውም
አገባት
፥
ዘርም
ሳይተው
ሞተ
፤
ሦስተኛውም
እንዲሁ
፤
22
ሰባቱም
አገቡአት
፥
ዘርም
አላስቀሩም
።
ከሁሉም
በኋላ
ሴቲቱ
ደግሞ
ሞተች
።
23
ሰባቱ
አግብተዋታልና
በትንሣኤ
ቀን
ሲነሡ
ከእነርሱ
ለማናቸው
ሚስት
ትሆናለች
?
24
ኢየሱስም
መልሶ
እንዲህ
አላቸው
።
መጻሕፍትንና
የእግዚአብሔርን
ኃይል
አታውቁምና
ስለዚህ
የምትስቱ
አይደለምን
?
25
ከሙታንስ
ሲነሡ
በሰማያት
እንዳሉ
መላእክት
ይሆናሉ
እንጂ
አያገቡም
፥
አይጋቡምም
።
26
ስለ
ሙታን
ግን
እንዲነሡ
እግዚአብሔር
።
እኔ
የአብርሃም
አምላክ
የይስሐቅም
አምላክ
የያዕቆብም
አምላክ
ነኝ
እንዳለው
በሙሴ
መጽሐፍ
በቍጥቋጦው
ዘንድ
የተጻፈውን
አላነበባችሁምን
?
27
የሕያዋን
አምላክ
ነው
እንጂ
የሙታን
አይደለም
።
እንግዲህ
እጅግ
ትስታላችሁ
።
28
ከጻፎችም
አንዱ
ቀርቦ
ሲከራከሩ
ሰማና
መልካም
አድርጎ
እንደ
መለሰላቸው
አስተውሎ
።
ከሁሉ
ፊተኛይቱ
ትእዛዝ
ማናቸይቱ
ናት
?
ብሎ
ጠየቀው
።
29
ኢየሱስም
መልሶ
እንዲህ
አለው
።
ከትእዛዛቱ
ሁሉ
ፊተኛይቱ
።
እስራኤል
ሆይ
፥
ስማ
፤
ጌታ
አምላካችን
አንድ
ጌታ
ነው
፥
30
አንተም
በፍጹም
ልብህ
በፍጹምም
ነፍስህ
በፍጹምም
አሳብህ
በፍጹምም
ኃይልህ
ጌታ
አምላክህን
ውደድ
የምትል
ናት
።
ፊተኛይቱ
ትእዛዝ
ይህች
ናት
።
31
ሁለተኛይቱም
።
ባልንጀራህን
እንደ
ራስህ
ውደድ
የምትል
እርስዋን
የምትመስል
ይህች
ናት
።
ከእነዚህ
የምትበልጥ
ሌላ
ትእዛዝ
የለችም
።
32
ጻፊውም
።
መልካም
ነው
፥
መምህር
ሆይ
፤
አንድ
ነው
ከእርሱም
በቀር
ሌላ
የለም
ብለህ
በእውነት
ተናገርህ
፤
33
በፍጹም
ልብ
በፍጹም
አእምሮም
በፍጹም
ነፍስም
በፍጹም
ኃይልም
እርሱን
መውደድ
፥
ባልንጀራንም
እንደ
ራስ
መውደድ
በሙሉ
ከሚቃጠል
መሥዋዕትና
ከሌላው
መሥዋዕት
ሁሉ
የሚበልጥ
ነው
አለው
።
34
ኢየሱስም
በአእምሮ
እንደ
መለሰ
አይቶ
።
አንተ
ከእግዚአብሔር
መንግሥት
የራቅህ
አይደለህም
አለው
።
ከዚህም
በኋላ
ማንም
ሊጠይቀው
አልደፈረም
።
35
ኢየሱስም
በመቅደስ
ሲያስተምር
መልሶ
እንዲህ
አለ
።
ጻፎች
ክርስቶስ
የዳዊት
ልጅ
ነው
እንዴት
ይላሉ
?
36
ዳዊት
ራሱ
በመንፈስ
ቅዱስ
።
ጌታ
ጌታዬን
።
ጠላቶችህን
የእግርህ
መረገጫ
እስካደርግልህ
ድረስ
በቀኜ
ተቀመጥ
አለው
አለ
።
37
ዳዊትም
ራሱ
ጌታ
አለው
፤
እንዴትስ
ልጁ
ይሆናል
?
ብዙ
ሕዝብም
በደስታ
ይሰሙት
ነበር
።
38-39
ሲያስተምርም
እንዲህ
አለ
።
ረጃጅም
ልብስ
ለብሰው
መዞርን
፥
በገበያም
ሰላምታን
፥
በምኵራብም
የከበሬታን
ወንበር
፥
በግብርም
የከበሬታን
ስፍራ
ከሚወዱ
ከጻፎች
ተጠበቁ
፤
40
የመበለቶችን
ቤት
የሚበሉ
ጸሎታቸውንም
በማስረዘም
የሚያመካኙ
እነዚህ
የባሰ
ፍርድ
ይቀበላሉ
።
41
ኢየሱስም
በመዝገብ
አንጻር
ተቀምጦ
ሕዝቡ
በመዝገብ
ውስጥ
ገንዘብ
እንዴት
እንዲጥሉ
ያይ
ነበር
፤
ብዙ
ባለ
ጠጎችም
ብዙ
ይጥሉ
ነበር
፤
42
አንዲትም
ድሀ
መበለት
መጥታ
አንድ
ሳንቲም
የሚያህሉ
ሁለት
ናስ
ጣለች
።
43
ደቀ
መዛሙርቱንም
ጠርቶ
።
እውነት
እላችኋለሁ
፥
በመዝገብ
ውስጥ
ከሚጥሉት
ሁሉ
ይልቅ
ይህች
ድሀ
መበለት
አብልጣ
ጣለች
፤
44
ሁሉ
ከትርፋቸው
ጥለዋልና
፥
ይህች
ግን
ከጕድለትዋ
የነበራትን
ሁሉ
ትዳርዋን
ሁሉ
ጣለች
አላቸው
።
13
1
እርሱም
ከመቅደስ
ሲወጣ
ከደቀ
መዛሙርቱ
አንዱ
።
መምህር
ሆይ
፥
እንዴት
ያሉ
ድንጋይዎችና
እንዴት
ያሉ
ሕንጻዎች
እንደ
ሆኑ
እይ
አለው
።
2
ኢየሱስም
መልሶ
።
እነዚህን
ታላላቅ
ሕንጻዎች
ታያለህን
?
ድንጋይ
በድንጋይ
ላይ
ሳይፈርስ
በዚህ
አይቀርም
አለው
።
3
በመቅደስም
ትይዩ
በደብረ
ዘይት
ተቀምጦ
ሳለ
፥
ጴጥሮስና
ያዕቆብ
ዮሐንስም
እንድርያስም
።
4
ንገረን
፥
ይህ
መቼ
ይሆናል
?
ይህስ
ሁሉ
ይፈጸም
ዘንድ
እንዳለው
ምልክቱ
ምንድር
ነው
?
ብለው
ለብቻቸው
ጠየቁት
።
5
ኢየሱስም
መልሶ
እንዲህ
ይላቸው
ጀመር
።
ማንም
እንዳያስታችሁ
ተጠንቀቁ
።
6
ብዙዎች
።
እኔ
ነኝ
እያሉ
በስሜ
ይመጣሉና
፥
ብዙዎችንም
ያስታሉ
።
7
ጦርንም
የጦርንም
ወሬ
በሰማችሁ
ጊዜ
አትደንግጡ
፤
ይህ
ሊሆን
ግድ
ነውና
፥
ነገር
ግን
መጨረሻው
ገና
ነው
።
8
ሕዝብ
በሕዝብ
ላይ
መንግሥትም
በመንግሥት
ላይ
ይነሣልና
፤
በልዩ
ልዩ
ስፍራ
የምድር
መናወጥ
ይሆናል
፤
ራብ
ይሆናል
፤
እነዚህ
የምጥ
ጣር
መጀመሪያ
ናቸው
።
9
እናንተ
ግን
ለራሳችሁ
ተጠንቀቁ
፤
ወደ
ሸንጎ
አሳልፈው
ይሰጡአችኋል
በምኵራብም
ትገረፋላችሁ
ምስክርም
ይሆንባቸው
ዘንድ
ስለ
እኔ
በገዥዎችና
በነገሥታት
ፊት
ትቆማላችሁ
።
10
አስቀድሞም
ወንጌል
ለአሕዛብ
ሁሉ
ይሰበክ
ዘንድ
ይገባል
።
11
ሲጐትቱአችሁና
አሳልፈው
ሲሰጡአችሁም
ምን
እንድትናገሩ
አስቀድማችሁ
አትጨነቁ
፥
ዳሩ
ግን
በዚያች
ሰዓት
የሚሰጣችሁን
ተናገሩ
፤
የሚነግረው
መንፈስ
ቅዱስ
ነው
እንጂ
እናንተ
አይደላችሁምና
።
12
ወንድምም
ወንድሙን
አባትም
ልጁን
ለሞት
አሳልፎ
ይሰጣል
፥
ልጆችም
በወላጆቻቸው
ላይ
ይነሣሉ
።
ይገድሉአቸውማል
፤
13
በሁሉም
ዘንድ
ስለ
ስሜ
የተጠላችሁ
ትሆናላችሁ
፤
እስከ
መጨረሻ
የሚጸና
ግን
እርሱ
ይድናል
።
14
ነገር
ግን
በነቢዩ
በዳንኤል
የተባለውን
የጥፋት
ርኵሰት
በማይገባው
ስፍራ
ቆሞ
ብታዩ
፥
አንባቢው
ያስተውል
፥
በዚያን
ጊዜ
በይሁዳ
ያሉ
ወደ
ተራሮች
ይሽሹ
፥
15
በሰገነትም
ያለ
ወደ
ቤት
አይውረድ
ከቤቱም
አንዳች
ይወስድ
ዘንድ
አይግባ
፥
16
በእርሻም
ያለ
ልብሱን
ይወስድ
ዘንድ
ወደ
ኋላው
አይመለስ
።
17
በዚያን
ወራትም
ለርጉዞችና
ለሚያጠቡ
ወዮላቸው
።
18
ነገር
ግን
ሽሽታችሁ
በክረምት
እንዳይሆን
ጸልዩ
፤
19
በዚያን
ወራት
እግዚአብሔር
ከፈጠረው
ከፍጥረት
መጀመሪያ
ጀምሮ
እስከ
አሁን
ድረስ
ያልሆነ
ደግሞም
የማይሆን
የመከራ
ዓይነት
ይሆናልና
።
20
ጌታስ
ወራቶቹን
ባያሳጥር
፥
ሥጋ
የለበሰ
ሁሉ
ባልዳነም
፤
ነገር
ግን
ስለ
መረጣቸው
ምርጦች
ወራቶቹን
አሳጠረ
።
21
በዚያን
ጊዜም
ማንም
።
እነሆ
፥
ክርስቶስ
ከዚህ
አለ
፥
ወይም
።
እነሆ
፥
ከዚያ
አለ
ቢላችሁ
አትመኑ
፤
22
ሐሰተኞች
ክርስቶሶችና
ሐሰተኞች
ነቢያት
ይነሣሉና
፥
ቢቻላቸውስ
የተመረጡትን
እንኳ
ያስቱ
ዘንድ
ምልክትና
ድንቅ
ያደርጋሉ
።
23
እናንተ
ግን
ተጠንቀቁ
፤
እነሆ
፥
አስቀድሜ
ሁሉን
ነገርኋችሁ
።
24
በዚያን
ወራት
ግን
ከዚያ
መከራ
በኋላ
ፀሐይ
ይጨልማል
ጨረቃም
ብርሃንዋን
አትሰጥም
፥
25
ከዋክብትም
ከሰማይ
ይወድቃሉ
፥
የሰማያትም
ኃይላት
ይናወጣሉ
።
26
በዚያን
ጊዜም
የሰው
ልጅ
በብዙ
ኃይልና
ክብር
በደመና
ሲመጣ
ያዩታል
።
27
በዚያን
ጊዜም
መላእክትን
ይልካል
ከአራቱ
ነፋሳትም
ከምድር
ዳርቻ
እስከ
ሰማይ
ዳርቻ
የተመረጡትን
ይሰበስባቸዋል
።
28
ምሳሌውንም
ከበለስ
ተማሩ
፤
ጫፍዋ
ሲለሰልስ
ቅጠልዋም
ሲያቈጠቍጥ
፥
ያን
ጊዜ
በጋ
እንደ
ቀረበ
ታውቃላችሁ
፤
29
እንዲሁ
ደግሞ
እናንተ
ይህን
ሁሉ
መሆኑን
ስታዩ
ቀርቦ
በደጅ
እንደ
ሆነ
እወቁ
።
30
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ይህ
ሁሉ
እስኪሆን
ድረስ
ይህ
ትውልድ
አያልፍም
።
31
ሰማይና
ምድር
ያልፋሉ
ቃሌ
ግን
አያልፍም
።
32
ስለዚያች
ቀን
ወይም
ስለዚያች
ሰዓት
ግን
የሰማይ
መላእክትም
ቢሆኑ
ልጅም
ቢሆን
ከአባት
በቀር
የሚያውቅ
የለም
።
33
ጊዜው
መቼ
እንዲሆን
አታውቁምና
ተጠንቀቁ
፤
ትጉ
፤
ጸልዩም
።
34
ቤቱን
ትቶ
ወደ
ሌላ
አገር
እንደ
ሄደ
ሰው
ነው
፥
ለባሮቹም
ሥልጣን
ለእያንዳንዱም
ሥራውን
ሰጥቶ
በረኛውን
እንዲተጋ
አዘዘ
።
35
እንግዲህ
በማታ
ቢሆን
ወይም
በእኩለ
ሌሊት
ወይም
ዶሮ
ሲጮኽ
ወይም
በማለዳ
ቢሆን
ባለቤቱ
መቼ
እንዲመጣ
አታውቁምና
36
ድንገት
መጥቶ
ተኝታችሁ
እንዳያገኛችሁ
ስለዚህ
ትጉ
።
37
ለእናንተም
የምነግራችሁ
ለሁሉ
እላለሁ
፤
ትጉ
።
14
1
ከሁለት
ቀን
በኋላ
ፋሲካና
የቂጣ
በዓል
ነበረ
።
የካህናት
አለቆችም
ጻፎችም
እንዴት
አድርገው
በተንኰል
እንደሚይዙትና
እንደሚገድሉት
ይፈልጉ
ነበር
።
2
የሕዝብ
ሁከት
እንዳይሆን
በበዓል
አይሁን
ይሉ
ነበርና
።
3
እርሱም
በቢታንያ
በለምጻሙ
በስምዖን
ቤት
በነበረ
ጊዜ
፥
በማዕድ
ተቀምጦ
ሳለ
፥
አንዲት
ሴት
ዋጋው
እጅግ
የከበረ
ጥሩ
ናርዶስ
ሽቱ
የመላበት
የአልባስጥሮስ
ቢልቃጥ
ይዛ
መጣች
፤
ቢልቃጡንም
ሰብራ
በራሱ
ላይ
አፈሰሰችው
።
4
አንዳንዶችም
።
ይህ
የሽቱ
ጥፋት
ለምንድር
ነው
?
5
ይህ
ሽቱ
ከሦስት
መቶ
ዲናር
በሚበልጥ
ዋጋ
ተሽጦ
ለድሆች
ሊሰጥ
ይቻል
ነበርና
ብለው
በራሳቸው
ይቈጡ
ነበር
፤
እርስዋንም
ነቀፉአት
።
6
ኢየሱስ
ግን
እንዲህ
አለ
።
ተዉአት
፤
ስለ
ምን
ታደክሙአታላችሁ
?
መልካም
ሥራ
ሠርታልኛለች
።
7
ድሆች
ሁልጊዜ
ከእናንተ
ጋር
ይኖራሉና
፥
በማናቸውም
በወደዳችሁት
ጊዜ
መልካም
ልታደርጉላቸው
ትችላላችሁ
፥
እኔ
ግን
ሁልጊዜ
ከእናንተ
ጋር
አልኖርም
።
8
የተቻላትን
አደረገች
፤
አስቀድማ
ለመቃብሬ
ሥጋዬን
ቀባችው
።
9
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ይህ
ወንጌል
በዓለሙ
ሁሉ
በሚሰበክበት
በማናቸውም
ስፍራ
፥
እርስዋ
ያደረገችው
ደግሞ
ለእርስዋ
መታሰቢያ
ሊሆን
ይነገራል
።
10
ከአሥራ
ሁለቱም
አንዱ
የአስቆሮቱ
ይሁዳ
አሳልፎ
ሊሰጠው
ወደ
ካህናት
አለቆች
ሄደ
።
11
ሲሰሙም
ደስ
አላቸው
ብርም
ይሰጡት
ዘንድ
ተስፋ
ሰጡት
።
በሚመች
ጊዜም
እንዴት
አድርጎ
አሳልፎ
እንዲሰጠው
ይፈልግ
ነበር
።
12
ፋሲካን
በሚያርዱበት
በቂጣ
በዓል
መጀመሪያ
ቀን
ደቀ
መዛሙርቱ
።
ፋሲካን
ትበላ
ዘንድ
ወዴት
ሄደን
ልናሰናዳ
ትወዳለህ
?
አሉት
።
13
ከደቀ
መዛሙርቱም
ሁለት
ላከ
እንዲህም
አላቸው
።
ወደ
ከተማ
ሂዱ
፥
ማድጋ
ውኃ
የተሸከመ
ሰውም
ይገናኛችኋል
፤
14
ተከተሉት
፥
የሚገባበትንም
የቤቱን
ጌታ
።
መምህሩ
።
ከደቀ
መዛሙርቴ
ጋር
ፋሲካን
የምበላበት
የእንግዳ
ቤት
ወዴት
ነው
?
ይላል
በሉት
።
15
እርሱም
በደርብ
ላይ
ያለውን
የተሰናዳና
የተነጠፈ
ታላቅ
አዳራሽ
ያሳያችኋል
፤
16
በዚያም
አሰናዱልን
።
ደቀ
መዛሙርቱም
ወጡ
ወደ
ከተማም
ሄደው
እንዳላቸው
አገኙ
፥
ፋሲካንም
አሰናዱ
።
17
በመሸም
ጊዜ
ከአሥራ
ሁለቱ
ጋር
መጣ
።
18
ተቀምጠውም
ሲበሉ
ኢየሱስ
።
እውነት
እላችኋለሁ
፥
ከእናንተ
አንዱ
፥
እርሱም
ከእኔ
ጋር
የሚበላው
አሳልፎ
ይሰጠኛል
አለ
።
19
እነርሱም
ያዝኑ
፥
እያንዳንዳቸውም
።
እኔ
እሆንን
?
ይሉት
ጀመር
።
20
እርሱም
መልሶ
።
ከአሥራ
ሁለቱ
አንዱ
ከእኔ
ጋር
ወደ
ወጭቱ
እጁን
የሚያጠልቀው
ነው
።
21
የሰው
ልጅስ
ስለ
እርሱ
እንደ
ተጻፈ
ይሄዳል
፤
ነገር
ግን
የሰው
ልጅ
አልፎ
ለሚሰጥበት
ለዚያ
ሰው
ወዮለት
፤
ያ
ሰው
ባልተወለደ
ይሻለው
ነበር
አላቸው
።
22
ሲበሉም
ኢየሱስ
እንጀራን
አንሥቶ
ባረከ
ቈርሶም
ሰጣቸውና
።
እንካችሁ
፤
ይህ
ሥጋዬ
ነው
አለ
።
23
ጽዋንም
አንሥቶ
አመስግኖም
ሰጣቸው
፥
ሁሉም
ከእርሱ
ጠጡ
።
24
እርሱም
።
ይህ
ስለ
ብዙዎች
የሚፈስ
የአዲስ
ኪዳን
ደሜ
ነው
።
25
እውነት
እላችኋለሁ
፥
በእግዚአብሔር
መንግሥት
ከወይኑ
ፍሬ
አዲሱን
እስከምጠጣበት
እስከዚያ
ቀን
ድረስ
ደግሞ
አልጠጣውም
አላቸው
።
26
መዝሙርም
ከዘመሩ
በኋላ
ወደ
ደብረ
ዘይት
ወጡ
።
27
ኢየሱስም
።
በዚች
ሌሊት
ሁላችሁ
በእኔ
ትሰናከላላችሁ
፤
እረኛዉን
እመታለሁ
በጎችም
ይበተናሉ
የሚል
ተጽፎአልና
።
28
ነገር
ግን
ከተነሣሁ
በኋላ
ወደ
ገሊላ
እቀድማችኋለሁ
አላቸው
።
29
ጴጥሮስም
።
ሁሉም
ቢሰናከሉ
እኔ
ግን
ከቶ
አልሰናከልም
አለው
።
30
ኢየሱስም
።
እውነት
እልሃለሁ
፥
ዛሬ
በዚች
ሌሊት
ዶሮ
ሁለት
ጊዜ
ሳይጮኽ
ሦስት
ጊዜ
ትክደኛለህ
አለው
።
31
እርሱም
ቃሉን
አበርትቶ
።
ከአንተ
ጋር
የምሞት
እንኳ
ቢሆን
ከቶ
አልክድህም
አለ
።
ሁሉም
ደግሞ
እንደዚሁ
አሉ
።
32
ጌቴሴማኒ
ወደምትባልም
ስፍራ
መጡ
፥
ደቀ
መዛሙርቱንም
።
ስጸልይ
ሳለሁ
፥
በዚህ
ተቀመጡ
አላቸው
።
33
ጴጥሮስንና
ያዕቆብን
ዮሐንስንም
ከእርሱ
ጋር
ወሰደ
፤
ሊደነግጥም
ሊተክዝም
ጀመረና
።
34
ነፍሴ
እስከ
ሞት
ድረስ
እጅግ
አዘነች
፤
በዚህ
ቈዩ
ትጉም
አላቸው
።
35
ጥቂትም
ወደ
ፊት
እልፍ
ብሎ
በምድርም
ወድቆ
፥
ይቻልስ
ቢሆን
ሰዓቲቱ
ከእርሱ
እንድታልፍ
ጸለየና
።
36
አባ
አባት
ሆይ
፥
ሁሉ
ይቻልሃል
፤
ይህችን
ጽዋ
ከእኔ
ውሰድ
፤
ነገር
ግን
አንተ
የምትወደው
እንጂ
እኔ
የምወደው
አይሁን
አለ
።
37
መጣም
ተኝተውም
አገኛቸው
፥
ጴጥሮስንም
።
ስምዖን
ሆይ
፥
ተኝተሃልን
?
አንዲት
ሰዓት
ስንኳ
ልትተጋ
አልቻልህምን
?
38
ወደ
ፈተና
እንዳትገቡ
ትጉ
ጸልዩም
፤
መንፈስስ
ተዘጋጅታለች
፥
ሥጋ
ግን
ደካማ
ነው
አለው
።
39
ደግሞም
ሄዶ
ያንኑ
ቃል
ጸለየ
።
40
ደግሞም
መጥቶ
ዓይኖቻቸው
በእንቅልፍ
ከብደው
ነበርና
ተኝተው
አገኛቸው
፥
የሚመልሱለትንም
አላወቁም
።
41
ሦስተኛም
መጥቶ
።
እንግዲህስ
ተኙ
ዕረፉም
፤
ይበቃል
፤
ሰዓቲቱ
ደረሰች
፤
እነሆ
፥
የሰው
ልጅ
በኃጢአተኞች
እጅ
አልፎ
ይሰጣል
።
42
ተነሡ
፥
እንሂድ
፤
እነሆ
፥
አሳልፎ
የሚሰጠኝ
ቀርቦአል
አላቸው
።
43
ወዲያውም
ገና
ሲናገር
ከአሥራ
ሁለቱ
አንዱ
ይሁዳ
መጣ
፥
ከእርሱም
ጋር
ብዙ
ሰዎች
ሰይፍና
ጐመድ
ይዘው
ከካህናት
አለቆችና
ከጻፎች
ከሽማግሌዎችም
ዘንድ
መጡ
።
44
አሳልፎ
የሚሰጠውም
።
የምስመው
እርሱ
ነው
፤
ያዙት
ተጠንቅቃችሁም
ውሰዱት
ብሎ
ምልክት
ሰጥቶአቸው
ነበር
።
45
መጥቶም
ወዲያው
ወደ
እርሱ
ቀረበና
።
መምህር
ሆይ
፥
መምህር
ሆይ
፥
ብሎ
ሳመው
፤
46
እነርሱም
እጃቸውን
በእርሱ
ላይ
ጭነው
ያዙት
።
47
በአጠገብ
ከቆሙት
ግን
አንዱ
ሰይፉን
መዞ
የሊቀ
ካህናቱን
ባሪያ
መታ
ጆሮውንም
ቈረጠ
።
48
ኢየሱስም
መልሶ
።
ወንበዴ
እንደምትይዙ
ሰይፍና
ጐመድ
ይዛችሁ
ልትይዙኝ
መጣችሁን
?
49
በመቅደስ
ዕለት
ዕለት
እያስተማርሁ
ከእናንተ
ጋር
ስኖር
አልያዛችሁኝም
፤
ነገር
ግን
መጻሕፍት
ይፈጸሙ
ዘንድ
ይህ
ሆነ
አላቸው
።
50
ሁሉም
ትተውት
ሸሹ
።
51
ዕርቃኑን
በነጠላ
የሸፈነ
አንድ
ጎበዝ
ይከተለው
ነበር
፥
52
ጎበዛዝቱም
ያዙት
፤
እርሱ
ግን
ነጠላውን
ትቶ
ዕራቁቱን
ሸሸ
።
53
ኢየሱስንም
ወደ
ሊቀ
ካህናቱ
ወሰዱት
፥
የካህናት
አለቆችም
ሁሉ
ሽማግሌዎችም
ጻፎችም
ተሰበሰቡ
።
54
ጴጥሮስም
እስከ
ሊቀ
ካህናቱ
ግቢ
ውስጥ
በሩቁ
ተከተለው
፥
ከሎሌዎችም
ጋር
ተቀምጦ
እሳት
ይሞቅ
ነበር
።
55
የካህናት
አለቆችም
ሸንጎውም
ሁሉ
እንዲገድሉት
በኢየሱስ
ላይ
ምስክር
ይፈልጉ
ነበር
፥
አላገኙምም
፤
56
ብዙዎች
በሐሰት
ይመሰክሩበት
ነበርና
፥
ምስክርነታቸው
ግን
አልተሰማማም
።
57-58
ሰዎችም
ተነሥተው
።
እኔ
ይህን
በእጅ
የተሠራውን
ቤተ
መቅደስ
አፈርሰዋለሁ
በሦስት
ቀንም
ሌላውን
በእጅ
ያልተሠራውን
እሠራለሁ
ሲል
ሰማነው
ብለው
በሐሰት
መሰከሩበት
።
59
ምስክርነታቸውም
እንዲሁ
እንኳ
አልተሰማማም
።
60
ሊቀ
ካህናቱም
በመካከላቸው
ተነሥቶ
።
አንዳች
አትመልስምን
?
እነዚህስ
በአንተ
ላይ
የሚመሰክሩብህ
ምንድር
ነው
?
ብሎ
ኢየሱስን
ጠየቀው
።
61
እርሱ
ግን
ዝም
አለ
አንዳችም
አልመለሰም
።
ደግሞ
ሊቀ
ካህናቱ
ጠየቀውና
።
የቡሩክ
ልጅ
ክርስቶስ
አንተ
ነህን
?
አለው
።
62
ኢየሱስም
።
እኔ
ነኝ
፤
የሰው
ልጅም
በኃይል
ቀኝ
ሲቀመጥ
በሰማይም
ደመና
ሲመጣ
ታያላችሁ
አለ
።
63
ሊቀ
ካህናቱም
ልብሱን
ቀደደና
።
ከእንግዲህ
ወዲህ
ምስክሮችን
ምን
ያስፈልገናል
?
64
ስድቡን
ሰማችሁ
፤
ምን
ይመስላችኋል
?
አለ
።
እነርሱም
ሁሉ
።
ሞት
ይገባዋል
ብለው
ፈረዱበት
።
65
አንዳንዶችም
ይተፉበት
ፊቱንም
ሸፍነው
ይጐስሙትና
።
ትንቢት
ተናገር
ይሉት
ጀመር
፤
ሎሌዎችም
በጥፊ
እየመቱ
ወሰዱት
።
66
ጴጥሮስም
በግቢ
ውስጥ
ወደ
ታች
ሳለ
ከሊቀ
ካህናቱ
ገረዶች
አንዲቱ
መጣች
፥
67
ጴጥሮስም
እሳት
ሲሞቅ
አይታ
ተመለከተችውና
።
አንተ
ደግሞ
ከናዝሬቱ
ከኢየሱስ
ጋር
ነበርህ
አለችው
።
68
እርሱ
ግን
።
የምትዪውን
አላውቅም
አላስተውልምም
ብሎ
ካደ
።
ወደ
ውጭም
ወደ
ደጅ
ወጣ
፤
ዶሮም
ጮኸ
።
69
ገረዲቱም
አይታው
በዚያ
ለቆሙት
።
ይህም
ከእነርሱ
ወገን
ነው
ስትል
ሁለተኛ
ትነግራቸው
ጀመር
።
70
እርሱም
ደግሞ
ካደ
።
ጥቂት
ቈይተውም
በዚያ
የቆሙት
ዳግመኛ
ጴጥሮስን
።
የገሊላ
ሰው
ነህና
ከእነርሱ
ወገን
በእውነት
ነህ
አሉት
።
71
እርሱ
ግን
።
ይህን
የምትሉትን
ሰው
አላውቀውም
ብሎ
ይረገምና
ይምል
ጀመር
።
ወዲያውም
ዶሮ
ሁለተኛ
ጮኸ
።
72
ጴጥሮስንም
ኢየሱስ
።
ዶሮ
ሁለት
ጊዜ
ሳይጮኽ
ሦስት
ጊዜ
ትክደኛለህ
ያለው
ቃል
ትዝ
አለው
፤
ነገሩንም
አስቦ
አለቀሰ
።
15
1
ወዲያውም
ማለዳ
የካህናት
አለቆች
ከሽማግሌዎችና
ከጻፎች
ከሸንጎውም
ሁሉ
ጋር
ከተማከሩ
በኋላ
፥
ኢየሱስን
አሳስረው
ወሰዱትና
ለጲላጦስ
አሳልፈው
ሰጡት
።
2
ጲላጦስም
።
አንተ
የአይሁድ
ንጉሥ
ነህን
?
ብሎ
ጠየቀው
።
እርሱም
።
አንተ
አልህ
ብሎ
መለሰለት
።
3
የካህናት
አለቆችም
ብዙ
ያሳጡት
ነበር
፤
እርሱ
ግን
ምንም
አልመለሰም
።
4
ጲላጦስም
ደግሞ
።
አንዳች
አትመልስምን
?
እነሆ
፥
በስንት
ነገር
ያሳጡሃል
ብሎ
ጠየቀው
።
5
ኢየሱስም
ከዚያ
በኋላ
ጲላጦስ
እስኪደነቅ
ድረስ
ምንም
አልመለሰም
።
6
በዚያም
በዓል
የለመኑትን
አንድ
እስረኛ
ይፈታላቸው
ነበር
።
7
በዓመፅም
ነፍስ
ከገደሉት
ከዓመፀኞች
ጋር
የታሰረ
በርባን
የተባለ
ነበረ
።
8
ሕዝቡም
ወጥተው
እንደ
ልማዱ
ያደርግላቸው
ዘንድ
እየጮኹ
ይለምኑት
ጀመር
።
9
ጲላጦስም
።
የአይሁድን
ንጉሥ
እፈታላችሁ
ዘንድ
ትወዳላችሁን
?
ብሎ
መለሰላቸው
፤
10
የካህናት
አለቆች
በቅንዓት
አሳልፈው
እንደ
ሰጡት
ያውቅ
ነበርና
።
11
የካህናት
አለቆች
ግን
በርባንን
በእርሱ
ፈንታ
ይፈታላቸው
ዘንድ
ሕዝቡን
አወኩአቸው
።
12
ጲላጦስም
ዳግመኛ
መልሶ
።
እንግዲህ
የአይሁድ
ንጉሥ
የምትሉትን
ምን
ላደርገው
ትወዳላችሁ
?
አላቸው
።
13
እነርሱም
ዳግመኛ
።
ስቀለው
እያሉ
ጮኹ
።
14
ጲላጦስም
።
ምን
ነው
?
ያደረገው
ክፋት
ምንድር
ነው
?
አላቸው
።
እነርሱ
ግን
።
ስቀለው
እያሉ
ጩኸት
አበዙ
።
15
ጲላጦስም
የሕዝቡን
ፈቃድ
ሊያደርግ
ወዶ
በርባንን
ፈታላቸው
፥
ኢየሱስንም
ገርፎ
እንዲሰቀል
አሳልፎ
ሰጠ
።
16
ወታደሮችም
ፕራይቶሪዮን
ወደሚባል
ግቢ
ውስጥ
ወሰዱት
፥
ጭፍራውንም
ሁሉ
በአንድነት
ጠሩ
።
17
ቀይ
ልብስም
አለበሱት
፥
የእሾህ
አክሊልም
ጎንጉነው
ደፉበት
፤
18
የአይሁድ
ንጉሥ
ሆይ
፥
ሰላም
ለአንተ
ይሁን
እያሉ
እጅ
ይነሱት
ጀመር
፤
19
ራሱንም
በመቃ
መቱት
ተፉበትም
፥
ተንበርክከውም
ሰገዱለት
።
20
ከተዘባበቱበትም
በኋላ
ቀዩን
ልብስ
ገፈፉት
፥
ልብሱንም
አለበሱት
፥
ሊሰቅሉትም
ወሰዱት
።
21
አንድ
መንገድ
አላፊም
የአሌክስንድሮስና
የሩፎስ
አባት
ስምዖን
የተባለ
የቀሬና
ሰው
ከገጠር
ሲመጣ
መስቀሉን
ይሸከም
ዘንድ
አስገደዱት
።
22
ትርጓሜውም
የራስ
ቅል
ስፍራ
ወደሚሆን
ጎልጎታ
ወደተባለ
ስፍራ
ወሰዱት
።
23
ከርቤም
የተቀላቀለበትን
የወይን
ጠጅ
እንዲጠጣ
ሰጡት
፤
እርሱ
ግን
አልተቀበለም
።
24
ሰቀሉትም
፥
ልብሱንም
ማን
ማን
እንዲወስድ
ዕጣ
ተጣጥለው
ተካፈሉ
።
25
በሰቀሉትም
ጊዜ
ሦስት
ሰዓት
ነበረ
።
26
የክሱ
ጽሕፈትም
።
የአይሁድ
ንጉሥ
የሚል
ተጽፎ
ነበር
።
27
ከእርሱም
ጋር
ሁለት
ወንበዶች
አንዱን
በቀኙ
አንዱንም
በግራው
ሰቀሉ
።
28
መጽሐፍም
።
ከአመፀኞች
ጋር
ተቆጠረ
ያለው
ተፈጸመ
።
29
የሚያልፉትም
ራሳቸውን
እየነቀነቁ
ይሰድቡት
ነበርና
።
ዋ
፥
ቤተ
መቅደስን
የምታፈርስ
በሦስት
ቀንም
የምትሠራ
፥
30
ከመስቀል
ወርደህ
ራስህን
አድን
አሉ
።
31
እንዲሁም
የካህናት
አለቆች
ደግሞ
ከጻፎች
ጋር
እርስ
በርሳቸው
እየተዘባበቱ
።
ሌሎችን
አዳነ
፤
ራሱን
ሊያድን
አይችልም
፤
32
አይተን
እናምን
ዘንድ
የእስራኤል
ንጉሥ
ክርስቶስ
አሁን
ከመስቀል
ይውረድ
አሉ
።
ከእርሱም
ጋር
የተሰቀሉት
ይነቅፉት
ነበር
።
33
ስድስት
ሰዓትም
በሆነ
ጊዜ
፥
እስከ
ዘጠኝ
ሰዓት
በምድር
ሁሉ
ላይ
ጨለማ
ሆነ
።
34
በዘጠኝ
ሰዓትም
ኢየሱስ
።
ኤሎሄ
፥
ኤሎሄ
፥
ላማ
ሰበቅታኒ
?
ብሎ
በታላቅ
ድምፅ
ጮኸ
፤
ትርጓሜውም
አምላኬ
፥
አምላኬ
፥
ለምን
ተውኸኝ
?
ማለት
ነው
።
35
በዚያም
ከቆሙት
ሰዎች
ሰምተው
።
እነሆ
፥
ኤልያስን
ይጠራል
አሉ
።
36
አንዱም
ሮጦ
ሆምጣጤ
በሰፍነግ
ሞላ
በመቃም
አድርጎ
።
ተዉ
፤
ኤልያስ
ሊያወርደው
ይመጣ
እንደ
ሆነ
እንይ
እያለ
አጠጣው
።
37
ኢየሱስም
በታላቅ
ድምፅ
ጮኸ
ነፍሱንም
ሰጠ
።
38
የቤተ
መቅደስም
መጋረጃ
ከላይ
እስከ
ታች
ከሁለት
ተቀደደ
።
39
በዚያም
በአንጻሩ
የቆመ
የመቶ
አለቃ
እንደዚህ
ጮኾ
ነፍሱን
እንደ
ሰጠ
ባየ
ጊዜ
።
ይህ
ሰው
በእውነት
የእግዚአብሔር
ልጅ
ነበረ
አለ
።
40-41
ሴቶችም
ደግሞ
በሩቅ
ሆነው
ይመለከቱ
ነበር
፤
ከእነርሱም
በገሊላ
ሳለ
ይከተሉትና
ያገለግሉት
የነበሩ
መግደላዊት
ማርያም
የታናሹ
ያዕቆብና
የዮሳም
እናት
ማርያም
ሰሎሜም
ነበሩ
፥
ከእርሱም
ጋር
ወደ
ኢየሩሳሌም
የወጡ
ሌሎች
ብዙዎች
ሴቶች
ነበሩ
።
42
አሁንም
በመሸ
ጊዜ
የሰንበት
ዋዜማ
የሆነ
የማዘጋጀት
ቀን
ስለ
ነበረ
፥
የከበረ
አማካሪ
የሆነ
የአርማትያስ
ዮሴፍ
መጣ
፥
43
እርሱም
ደግሞ
የእግዚአብሔርን
መንግሥት
ይጠባበቅ
ነበር
፤
ደፍሮም
ወደ
ጲላጦስ
ገባና
የኢየሱስን
ሥጋ
ለመነው
።
44
ጲላጦስም
አሁኑን
እንዴት
ሞተ
ብሎ
ተደነቀ
፥
የመቶ
አለቃውንም
ጠርቶ
ከሞተ
ቆይቶአልን
?
ብሎ
ጠየቀው
፤
45
ከመቶ
አለቃውም
ተረድቶ
በድኑን
ለዮሴፍ
ሰጠው
።
46
በፍታም
ገዝቶ
አውርዶም
በበፍታ
ከፈነው
ከዓለትም
በተወቀረ
መቃብር
አኖረው
፥
በመቃብሩ
ደጃፍም
ድንጋይ
አንከባለለ
።
47
መግደላዊትም
ማርያም
የዮሳም
እናት
ማርያም
ወዴት
እንዳኖሩት
ይመለከቱ
ነበር
።
16
1
ሰንበትም
ካለፈ
በኋላ
መግደላዊት
ማርያም
የያዕቆብም
እናት
ማርያም
ሰሎሜም
መጥተው
ሊቀቡት
ሽቱ
ገዙ
።
2
ከሳምንቱም
በፊተኛው
ቀን
እጅግ
በማለዳ
ፀሐይ
ከወጣ
በኋላ
ወደ
መቃብር
መጡ
።
3
እርስ
በርሳቸውም
።
ድንጋዩን
ከመቃብር
ደጃፍ
ማን
ያንከባልልልናል
?
ይባባሉ
ነበር
፤
4
ድንጋዩ
እጅግ
ትልቅ
ነበርና
፤
አሻቅበውም
አይተው
ድንጋዩ
ተንከባሎ
እንደ
ነበር
ተመለከቱ
።
5
ወደ
መቃብሩም
ገብተው
ነጭ
ልብስ
የተጎናጸፈ
ጎልማሳ
በቀኝ
በኩል
ተቀምጦ
አዩና
ደነገጡ
።
6
እርሱ
ግን
።
አትደንግጡ
፤
የተሰቀለውን
የናዝሬቱን
ኢየሱስን
ትፈልጋላችሁ
፤
ተነሥቶአል
፥
በዚህ
የለም
፤
እነሆ
እርሱን
ያኖሩበት
ስፍራ
።
7
ነገር
ግን
ሄዳችሁ
ለደቀ
መዛሙርቱ
ለጴጥሮስም
።
ወደ
ገሊላ
ይቀድማችኋል
፤
እንደ
ነገራችሁ
በዚያ
ታዩታላችሁ
ብላችሁ
ንገሩአቸው
አላቸው
።
8
መንቀጥቀጥና
መደንገጥ
ይዞአቸው
ነበርና
ወጥተው
ከመቃብር
ሸሹ
፤
ይፈሩ
ነበርና
ለማንም
አንዳች
አልነገሩም
።
እነርሱም
ያዘዛቸውን
ሁሉ
ለጴጥሮስና
ከእርሱ
ጋር
ላሉት
በአጭሩ
ተናገሩ
።
ከዚህም
በኋላ
ኢየሱስ
ራሱ
ለዘላለም
ድኅነት
የሆነውን
የማይለወጠውን
ቅዱስ
ወንጌል
ከፀሐይ
መውጫ
እስከ
መጥለቂያው
ድረስ
በእጃቸው
ላከው
።
9
ከሳምንቱም
በመጀመሪያው
ቀን
ማልዶ
በተነሣ
ጊዜ
፥
አስቀድሞ
ሰባት
አጋንንት
ላወጣላት
ለመግደላዊት
ማርያም
ታየ
።
10
እርስዋ
ሄዳ
ከእርሱ
ጋር
ሆነው
ለነበሩት
ሲያዝኑና
ሲያለቅሱ
ሳሉ
አወራችላቸው
፤
11
እነርሱም
ሕያው
እንደ
ሆነ
ለእርስዋም
እንደ
ታያት
ሲሰሙ
አላመኑም
።
12
ከዚህም
በኋላ
ከእነርሱ
ለሁለቱ
ወደ
ባላገር
ሲሄዱ
በመንገድ
በሌላ
መልክ
ተገለጠ
፤
13
እነርሱም
ሄደው
ለሌሎቹ
አወሩ
፤
እነዚያንም
ደግሞ
አላመኑአቸውም
።
14
ኋላም
በማዕድ
ተቀምጠው
ሳሉ
ለአሥራ
አንዱ
ተገለጠ
፥
ተነሥቶም
ያዩትን
ስላላመኑአቸው
አለማመናቸውንና
የልባቸውን
ጥንካሬ
ነቀፈ
።
15
እንዲህም
አላቸው
።
ወደ
ዓለም
ሁሉ
ሂዱ
ወንጌልንም
ለፍጥረት
ሁሉ
ስበኩ
።
16
ያመነ
የተጠመቀም
ይድናል
፥
ያላመነ
ግን
ይፈረድበታል
።
17
ያመኑትንም
እነዚህ
ምልክቶች
ይከተሉአቸዋል
፤
በስሜ
አጋንንትን
ያወጣሉ
፤
በአዲስ
ቋንቋ
ይናገራሉ
፤
እባቦችን
ይይዛሉ
፥
18
የሚገድልም
ነገር
ቢጠጡ
አይጎዳቸውም
፤
እጃቸውን
በድውዮች
ላይ
ይጭናሉ
እነርሱም
ይድናሉ
።
19
ጌታ
ኢየሱስም
ከእነርሱ
ጋር
ከተናገረ
በኋላ
ወደ
ሰማይ
ዐረገ
በእግዚአብሔርም
ቀኝ
ተቀመጠ
።
20
እነርሱም
ወጥተው
በየስፍራው
ሁሉ
ሰበኩ
፥
ጌታም
ከእነርሱ
ጋር
ይሠራ
ነበር
፥
በሚከተሉትም
ምልክቶች
ቃሉን
ያጸና
ነበር
።