የማርቆስ ወንጌል (Mark)


1

1 የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል መጀመሪያ

2-3 እነሆመንገድህን የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ሰው ድምፅ ተብሎ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደ ተጻፈ

4 ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ

5 የይሁዳም አገር ሁሉ የኢየሩሳሌምም ሰዎች ሁሉ ወደ እርሱ ይወጡ ነበርኃጢአታቸውንም እየተናዘዙ በዮርዳኖስ ወንዝ ከእርሱ ይጠመቁ ነበር

6 ዮሐንስም የግመል ጠጉር ለብሶ በወገቡ ጠፍር ይታጠቅ አንበጣና የበረሀ ማርም ይበላ ነበር

7 ተጎንብሼ የጫማውን ጠፍር መፍታት የማይገባኝ ከእኔ የሚበረታ በኋላዬ ይመጣል

8 እኔ በውኃ አጠመቅኋችሁ እርሱ ግን በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል እያለ ይሰብክ ነበር

9 በዚያ ወራትም ኢየሱስ ከገሊላ ናዝሬት መጥቶ ከዮሐንስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ

10 ወዲያውም ከውኃው በወጣ ጊዜ ሰማያት ሲቀደዱ መንፈስም እንደ ርግብ ሲወርድበት አየናየምወድህ ልጄ አንተ ነህ

11 በአንተ ደስ ይለኛል የሚል ድምፅ ከሰማያት መጣ

12 ወዲያውም መንፈስ ወደ ምድረ በዳ አወጣው

13 በምድረ በዳም ከሰይጣን እየተፈተነ አርባ ቀን ሰነበተ ከአራዊትም ጋር ነበረመላእክቱም አገለገሉት

14-15 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ወንጌል እየሰበከናዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች ንስሐ ግቡ በወንጌልም እመኑ እያለ ወደ ገሊላ መጣ

16 በገሊላ ባሕርም አጠገብ ሲያልፍ ስምዖንን ወንድሙንም እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየዓሣ አጥማጆች ነበሩና

17 ኢየሱስምበኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ አላቸው

18 ወዲያውም መረባቸውን ትተው ተከተሉት

19 ከዚያም ጥቂት እልፍ ብሎ የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ደግሞ በታንኳ ላይ መረባቸውን ሲያበጁ አየ

20 ወዲያውም ጠራቸው አባታቸውንም ዘብዴዎስን ከሞያተኞቹ ጋር በታንኳ ላይ ትተው ተከትለውት ሄዱ

21 ወደ ቅፍርናሆምም ገቡወዲያውም በሰንበት ወደ ምኵራብ ገብቶ አስተማረ

22 እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበር እንጂ እንደ ጻፎች አይደለምና በትምህርቱ ተገረሙ

23 በዚያን ጊዜም በምኩራባቸው ርኵስ መንፈስ ያለው ሰው ነበረ

24 እርሱምየናዝሬቱ ኢየሱስ ሆይከአንተ ጋር ምን አለን ? ልታጠፋን መጣህን ? ማን እንደ ሆንህ አውቄአለሁየእግዚአብሔር ቅዱሱ ብሎ ጮኸ

25 ኢየሱስምዝም በል ከእርሱም ውጣ ብሎ ገሠጸው

26 ርኵሱም መንፈስ አንፈራገጠውና በታላቅ ድምፅ ጮኾ ከእርሱ ወጣ

27 ሁሉምይህ ምንድር ነው ? በሥልጣን ርኵሳን መናፍስትን ያዝዛልእነርሱም ይታዘዙለታልና ይህ አዲስ ትምህርት ምንድር ነው ? ብለው እስኪጠያየቁ ድረስ አደነቁ

28 ዝናውም ወዲያው በየስፍራው ወደ ገሊላ ዙሪያ ሁሉ ወጣ

29 ወዲያውም ከምኵራብ ወጥቶ ከያዕቆብና ከዮሐንስ ጋር ወደ ስምዖንና ወደ እንድርያስ ቤት ገባ

30 የስምዖንም አማት በንዳድ ታማ ተኝታ ነበርስለ እርስዋም ወዲያው ነገሩት

31 ቀርቦም እጅዋን ይዞ አስነሣት ንዳዱም ወዲያው ለቀቃትና አገለገለቻቸው

32 ፀሐይም ገብቶ በመሸ ጊዜየታመሙትንና አጋንንት ያደረባቸውን ሁሉ ወደ እርሱ አመጡ

33 ከተማይቱም ሁላ በደጅ ተሰብስባ ነበር

34 በልዩ ልዩ ደዌም የታመሙትን ብዙዎችን ፈወሰብዙዎችንም አጋንንት አወጣአጋንንትም ክርስቶስ መሆኑን አውቀው ነበርና ሊናገሩ አልፈቀደላቸውም

35 ማለዳም ተነሥቶ ገና ሌሊት ሳለ ወጣ ወደ ምድረ በዳም ሄዶ በዚያ ጸለየ

36 ስምዖንና ከእርሱ ጋር የነበሩትም ገሥግሠው ተከተሉት

37 ባገኙትም ጊዜሁሉ ይፈልጉሃል አሉት

38 እርሱምበዚያ ደግሞ ልሰብክ ወደ ሌላ ስፍራ በቅርብ ወዳሉ መንደሮች እንሂድ ስለዚህ ወጥቻለሁና አላቸው

39 በምኵራባቸውም እየሰበከ አጋንንትንም እያወጣ ወደ ገሊላ ሁሉ መጣ

40 ለምጻምም ወደ እርሱ መጥቶ ተንበረከከናብትወድስ ልታነጻኝ ትችላለህ ብሎ ለመነው

41 ኢየሱስም አዘነለት እጁንም ዘርግቶ ዳሰሰውናእወድዳለሁንጻ አለው

42 በተናገረም ጊዜ ለምጹ ወዲያው ለቀቀውና ነጻ

43 በብርቱም ተናግሮ ወዲያው አወጣው

44 ለማንም አንዳች እንዳትናገር ተጠንቀቅነገር ግን ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ ለእነርሱም ምስክር እንዲሆን ስለ መንጻትህ ሙሴ ያዘዘውን አቅርብ አለው

45 እርሱ ግን ሲወጣ ብዙ ሊሰብክና ነገሩን ሊያወራ ጀመረስለዚህም ኢየሱስ ተገልጦ ወደ ከተማ መግባት ወደ ፊት ተሳነውነገር ግን በውጭ በምድረ በዳ ይኖር ነበርከየስፍራውም ወደ እርሱ ይመጡ ነበር

2

1 ከጥቂት ቀን በኋላ ወደ ቅፍርናሆም ደግሞ ገብቶ በቤት እንደ ሆነ ተሰማ

2 በደጅ ያለው ስፍራም እስኪጠባቸው ድረስ ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡቃሉንም ይነግራቸው ነበር

3 አራት ሰዎችም የተሸከሙትን ሽባ አመጡለት

4 ስለ ሕዝቡም ብዛት ወደ እርሱ ማቅረብ ቢያቅታቸው እርሱ ያለበትን የቤቱን ጣራ አነሡነድለውም ሽባው የተኛበትን አልጋ አወረዱ

5 ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውንአንተ ልጅኃጢአትህ ተሰረየችልህ አለው

6 ከጻፎችም አንዳንዶቹ በዚያ ተቀምጠው ነበር በልባቸውምይህ ሰው ስለ ምን እንደዚህ ያለ ስድብ ይናገራል ?

7 ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ኃጢአት ሊያስተሰርይ ማን ይችላል ? ብለው አሰቡ

8 ወዲያውም ኢየሱስ በልባቸው እንዲህ እንዳሰቡ በመንፈስ አውቆ እንዲህ አላቸውበልባችሁ ይህን ስለ ምን ታስባላችሁ ?

9 ሽባውንኃጢአትህ ተሰረየችልህ ከማለት ወይስተነሣ አልጋህንም ተሸከምና ሂድ ከማለት ማናቸው ይቀላል ?

10 ነገር ግን ለሰው ልጅ በምድር ላይ ኃጢአትን ሊያስተሰርይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ

11 ሽባውንአንተን እልሃለሁተነሣአልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ አለው

12 ተነሥቶም ወዲያው አልጋውን ተሸክሞ በሁሉ ፊት ወጣስለዚህም ሰዎች ሁሉ ተገረሙናእንዲህ ያለ ከቶ አላየንም ብለው እግዚአብሔርን አከበሩ

13 ደግሞም በባሕር አጠገብ ወጣሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ መጡና አስተማራቸው

14 ሲያልፍም በመቅረጫው ተቀምጦ የነበረውን የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን አየናተከተለኝ አለውተነሥቶም ተከተለው

15 በቤቱም በማዕድ ተቀምጦ ሳለብዙ ቀራጮችና ኃጢአተኞች ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ተቀመጡብዙ ነበሩ ይከተሉትም ነበር

16 ጻፎችና ፈሪሳውያንም ከቀራጮችና ከኃጢአተኞች ጋር ሲበላ አይተው ለደቀ መዛሙርቱከቀራ ጮችና ከኃጢአተኞች ጋር የሚበላና የሚጠጣ ስለ ምንድር ነው ? አሉ

17 ኢየሱስም ሰምቶሕመምተኞች እንጂ ብርቱዎች ባለ መድኃኒት አያስፈልጋቸውም ኃጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ልጠራ አልመጣሁም አላቸው

18 የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና ፈሪሳውያን ይጦሙ ነበርመጥተውምየዮሐንስና የፈሪሳውያን ደቀ መዛሙርት የሚጦሙት የአንተ ደቀ መዛሙርት ግን የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው ? አሉት

19 ኢየሱስም አላቸውሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሚዜዎች ሊጦሙ ይችላሉን ? ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊጦሙ አይችሉም

20 ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣልበዚያ ወራትም ይጦማሉ

21 በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚጥፍ የለምቢደረግ ግንአዲሱ መጣፊያ አሮጌውን ይቦጭቀዋልመቀደዱም የባሰ ይሆናል

22 በአረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለምቢደረግ ግንየወይን ጠጁ አቁማዳውን ያፈነዳል የወይኑም ጠጅ ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ያኖራሉ

23 በሰንበትም በእርሻ መካከል ሲያልፍ ደቀ መዛሙርቱ እየሄዱ እሸት ይቀጥፉ ጀመር

24 ፈሪሳውያንምእነሆበሰንበት ያልተፈቀደውን ስለ ምን ያደርጋሉ ? አሉት

25 እርሱምዳዊት ባስፈለገውና በተራበ ጊዜእርሱ አብረውት ከነበሩት ጋር ያደረገውንአብያተር ሊቀ ካህናት በነበረ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ

26 ከካህናት በቀር መብላት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕትን እንጀራ እንደ በላከእርሱም ጋር ለነበሩት እንደ ሰጣቸው ከቶ አላነበባችሁምን ? አላቸው

27 ደግሞሰንበት ስለ ሰው ተፈጥሮአል እንጂ ሰው ስለ ሰንበት አልተፈጠረም

28 እንዲሁም የሰው ልጅ ለሰንበት እንኳ ጌታዋ ነው አላቸው

3

1 ደግሞም ወደ ምኵራብ ገባበዚያም እጁ የሰለለች ሰው ነበር

2 ሊከሱትምበሰንበት ይፈውሰው እንደ ሆነ ይጠባበቁት ነበር

3 እጁ የሰለለችውንም ሰውተነሥተህ ወደ መካከል አለው

4 በሰንበት በጎ ማድረግ ተፈቅዶአልን ? ወይስ ክፉ ? ነፍስ ማዳን ወይስ መግደል ? አላቸውእነርሱም ዝም አሉ

5 ስለ ልባቸውም ድንዛዜ አዝኖ ዙሪያውን እየተመለከተ በቍጣ አያቸውሰውየውንምእጅህን ዘርጋ አለው

6 ዘረጋትምእጁም ዳነችፈሪሳውያንም ወጥተው ወዲያው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ከሄሮድስ ወገን ጋር ተማከሩበት

7 ኢየሱስም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ወደ ባህር ፈቀቅ አለከገሊላ የመጡም ብዙ ሰዎች ተከተሉት

8 እንዴት ትልቅ ነገርም እንዳደረገው ሰምተው ብዙ ሰዎች ከይሁዳ ከኢየሩሳሌምም ከኤዶምያስም ከዮርዳኖስ ማዶም ከጢሮስና ከሲዶና ምድርም ወደ እርሱ መጡ

9 ሰዎቹም እንዳያጋፉት ታንኳን ያቆዩለት ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን አዘዛቸው

10 ብዙ ሰዎችን አድኖ ነበርናስለዚህም ሥቃይ ያለባቸው ሁሉ እንዲዳስሱት ይወድቁበት ነበር

11 ርኵሳን መናፍስትም ባዩት ጊዜ በፊቱ ተደፍተውአንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ እያሉ ጮኹ

12 እንዳይገልጡትም በጣም አዘዛቸው

13 ወደ ተራራም ወጣራሱም የወደዳቸውን ወደ እርሱ ጠራወደ እርሱም ሄዱ

14 ከእርሱም ጋር እንዲኖሩና ለመስበክ እንዲልካቸው

15 ድውዮችንም ሊፈውሱ አጋንንትንም ሊያወጡ ሥልጣን ይሆንላቸው ዘንድ አሥራ ሁለት አደረገ

16 ስምዖንንም ጴጥሮስ ብሎ ሰየመው

17 የዘብዴዎስንም ልጅ ያዕቆብን የያዕቆብንም ወንድም ዮሐንስን ቦአኔርጌስ ብሎ ሰየማቸውየነጎድጓድ ልጆች ማለት ነው

18 እንድርያስንም ፊልጶስንም በርተሎሜውስንም ማቴዎስንም ቶማስንም የእልፍዮስን ልጅ ያዕቆብንም ታዴዎስንም ቀነናዊውንም ስምዖንን

19 አሳልፎ የሰጠውንም የአስቆሮቱን ይሁዳን

20 ወደ ቤትም መጡእንጀራም መብላት ስንኳ እስኪሳናቸው ድረስ እንደ ገና ብዙ ሰዎች ተሰበሰቡ

21 ዘመዶቹም ሰምተውአበደ ብለዋልና ሊይዙት ወጡ

22 ከኢየሩሳሌም የወረዱ ጻፎችምብዔል ዜቡል አለበትደግሞበአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል ብለው ተናገሩ

23 እነርሱንም ወደ እርሱ ጠርቶ በምሳሌ አላቸውሰይጣን ሰይጣንን ሊያወጣው እንዴት ይችላል ?

24 መንግሥትም እርስ በርስዋ ከተለያየች ያች መንግሥት ልትቆም አትችልም

25 ቤትም እርስ በርሱ ከተለያየ ቤት ሊቆም አይችልም

26 ሰይጣንም ራሱን ተቃውሞ ከተለያየመጨረሻ ይሆንበታል እንጂ ሊቆም አይችልም

27 ነገር ግን አስቀድሞ ኃይለኛውን ሳያስር ወደ ኃይለኛው ቤት ገብቶ ዕቃውን ሊበዘብዝ የሚችል የለምከዚያም ወዲያ ቤቱን ይበዘብዛል

28 እውነት እላችኋለሁለሰው ልጆች ኃጢአት ሁሉ የሚሳደቡትም ስድብ ሁሉ ይሰረይላቸዋል

29 በመንፈስ ቅዱስ ላይ የሚሳደብ ሁሉ ግን የዘላለም ኃጢአት ዕዳ ይሆንበታል እንጂ ለዘላለም አይሰረይለትም

30 ርኵስ መንፈስ አለበት ይሉ ነበርና

31 እናቱና ወንድሞቹም መጡ በውጭም ቆመው ወደ እርሱ ልከው አስጠሩት

32 ብዙ ሰዎችም በዙሪያው ተቀምጠው ነበሩናእነሆእናትህ ወንድሞችህም በውጭ ቆመው ይፈልጉሃል አሉት

33 መልሶምእናቴ ማን ናት ? ወንድሞቼስ እነ ማን ናቸው ? አላቸው

34 በዙሪያው ተቀምጠው ወደ ነበሩትም ተመለከተናእነሆ እናቴ ወንድሞቼም

35 የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉእርሱ ወንድሜ ነው እኅቴም እናቴም አለ

4

1 ደግሞም በባሕር ዳር ሊያስተምር ጀመረእጅግ ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ ስለ ተሰበሰቡ እርሱ በታንኳ ገብቶ በባሕር ላይ ተቀመጠሕዝቡም ሁሉ በባሕር ዳር በምድር ላይ ነበሩ

2 በምሳሌም ብዙ ያስተምራቸው ነበርበትምህርቱም አላቸውስሙ

3-4 እነሆዘሪ ሊዘራ ወጣሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀና ወፎች መጥተው በሉት

5 ሌላውም ብዙ መሬት በሌለበት በጭንጫ ላይ ወደቀና ጥልቅ መሬት ስላልነበረው ወዲያው በቀለ

6 ፀሐይም ሲወጣ ጠወለገሥርም ስላልነበረው ደረቀ

7 ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀእሾህም ወጣና አነቀውፍሬም አልሰጠም

8 ሌላውም በመልካም መሬት ላይ ወደቀና ወጥቶ አድጎ ፍሬ ሰጠአንዱም ሠላሳ አንዱም ስድሳ አንዱም መቶ አፈራ

9 የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ አለ

10 ብቻውንም በሆነ ጊዜበዙሪያው የነበሩት ከአሥራ ሁለቱ ጋር ስለ ምሳሌው ጠየቁት

11-12 እንዲህም አላቸውለእናንተ የእግዚአብሔርን መንግሥት ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋልበውጭ ላሉት ግንአይተው እንዲያዩ እንዳይመለከቱምሰምተውም እንዲሰሙ እንዳያስተውሉምእንዳይመለሱ ኃጢአታቸውም እንዳይሰረይላቸው ነገር ሁሉ በምሳሌ ይሆንባቸዋል

13 አላቸውምይህን ምሳሌ አታውቁምን ? እንዴትስ ምሳሌዎቹን ሁሉ ታውቃላችሁ ?

14 ዘሪው ቃሉን ይዘራልቃልም በተዘራበት በመንገድ ዳር የሆኑት እነዚህ ናቸው

15 በሰሙት ጊዜም ሰይጣን ወዲያው መጥቶ በልባቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል

16 እንዲሁም በጭንጫ ላይ የተዘሩት እነዚህ ናቸውቃሉንም ሰምተው ወዲያው በደስታ ይቀበሉታል

17 ለጊዜውም ነው እንጂ በእነርሱ ሥር የላቸውምኋላም በቃሉ ምክንያት መከራ ወይም ስደት በሆነ ጊዜ ወዲያው ይሰናከላሉ

18 በእሾህም የተዘሩት ሌሎች ናቸውቃሉን የሰሙት እነዚህ ናቸው

19 የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት ማታለል የሌላውም ነገር ምኞት ገብተው ቃሉን ያንቃሉየማያፈራም ይሆናል

20 በመልካምም መሬት የተዘሩት ቃሉን ሰምተው የሚቀበሉት አንዱም ሠላሳ አንዱም ስድሳ አንዱም መቶ ፍሬ የሚያፈሩት እነዚህ ናቸው

21 እንዲህም አላቸውመብራትን ከዕንቅብ ወይስ ከአልጋ በታች ሊያኖሩት ያመጡታልን ? በመቅረዝ ላይ ሊያኖሩት አይደለምን ?

22 እንዲገለጥ ባይሆን የተሰወረ የለምናወደ ግልጥ እንዲመጣ እንጂ የተሸሸገ የለም

23 የሚሰማ ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ

24 አላቸውምምን እንድትሰሙ ተጠበቁበምትሰፍሩበት መስፈሪያ ይሰፈርላችኋል ለእናንተም ይጨመርላችኋል

25 ላለው ይሰጠዋልናከሌለውም ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል

26 እርሱም አለበምድር ዘርን እንደሚዘራ ሰው የእግዚአብሔር መንግሥት እንደዚህ ናት ሌሊትና ቀን ይተኛልም ይነሣልም

27 እርሱም እንዴት እንደሚሆን ሳያውቅ ዘሩ ይበቅላል ያድግማል

28 ምድሪቱም አውቃ በመጀመሪያ ቡቃያ ኋላም ዛላ ኋላም በዛላው ፍጹም ሰብል ታፈራለች

29 ፍሬ ግን ሲበስል መከር ደርሶአልና ወዲያው ማጭድ ይልካል

30 እርሱም አለየእግዚአብሔርን መንግሥት በምን እናስመስላታለን ? ወይስ በምን ምሳሌ እንመስላታለን ?

31 እንደ ሰናፍጭ ቅንጣት ናትእርስዋም በምድር በተዘራች ጊዜ በምድር ካለ ዘር ሁሉ ታንሳለችበተዘራችም ጊዜ ትወጣለች ከአትክልትም ሁሉ የምትበልጥ ትሆናለች

32 የሰማይ ወፎችም በጥላዋ ሊሰፍሩ እስኪችሉ ታላላቅ ቅርንጫፎች ታደርጋለች

33 መስማትም በሚችሉበት መጠን እነዚህን በሚመስል በብዙ ምሳሌ ቃሉን ይነግራቸው ነበርያለ ምሳሌ ግን አልነገራቸውም

34 ለብቻቸውም ሲሆኑ ነገሩን ሁሉ ለገዛ ደቀ መዛሙርቱ ይፈታላቸው ነበር

35 በዚያም ቀን በመሸ ጊዜወደ ማዶ እንሻገር አላቸው

36 ሕዝቡንም ትተው በታንኳ እንዲያው ወሰዱትሌሎች ታንኳዎችም ከእርሱ ጋር ነበሩ

37 ብርቱ ዐውሎ ነፋስም ተነሣና ውኃ በታንኳይቱ እስኪሞላ ድረስ ማዕበሉ በታንኳይቱ ይገባ ነበር

38 እርሱም በስተኋላዋ ትራስ ተንተርሶ ተኝቶ ነበርአንቅተውምመምህር ሆይስንጠፋ አይገድህምን ? አሉት

39 ነቅቶም ነፋሱን ገሠጸው ባሕሩንምዝም በልፀጥ በል አለውነፋሱም ተወ ታላቅ ፀጥታም ሆነ

40 እንዲህ የምትፈሩ ስለ ምን ነው ? እንዴትስ እምነት የላችሁም ? አላቸው

41 እጅግም ፈሩናእንግዲህ ነፋስም ባሕርም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው ? ተባባሉ

5

1 ወደ ባሕር ማዶም ወደ ጌርጌሴኖን አገር መጡ

2 ከታንኳይቱም በወጣ ጊዜርኵስ መንፈስ የያዘው ሰው ከመቃብር ወጥቶ ወዲያው ተገናኘው

3 እርሱም በመቃብር ይኖር ነበርበሰንሰለትም ስንኳ ማንም ሊያስረው በዚያን ጊዜ አይችልም ነበር

4 ብዙ ጊዜ በእግር ብረትና በሰንሰለት ይታሰር ነበርና ዳሩ ግን ሰንሰለቱን ይበጣጥስ እግር ብረቱንም ይሰባብር ነበርሊያሸንፈውም የሚችል አልነበረም

5 ሁልጊዜም ሌሊትና ቀን በመቃብርና በተራራ ሆኖ ይጮኽ ነበር ሰውነቱንም በድንጋይ ይቧጭር ነበር

6 ኢየሱስንም ከሩቅ ባየ ጊዜ ሮጦ ሰገደለት

7 በታላቅ ድምፅም እየጮኸየልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይከአንተ ጋር ምን አለኝ ? እንዳታሠቃየኝ በእግዚአብሔር አምልሃለሁ አለ

8 አንተ ርኵስ መንፈስከዚህ ሰው ውጣ ብሎት ነበርና

9 ስምህ ማን ነው ? ብሎ ጠየቀውብዙዎች ነንና ስሜ ሌጌዎን ነው አለው

10 ከአገርም ውጭ እንዳይሰዳቸው አጥብቆ ለመነው

11 በዚያም በተራራ ጥግ ብዙ የእሪያ መንጋ ይሰማራ ነበርና

12 ወደ እሪያዎቹ እንድንገባ ስደደን ብለው ለመኑት

13 ኢየሱስም ፈቀደላቸውርኵሳን መናፍስቱም ወጥተው ወደ እሪያዎቹ ገቡሁለት ሺህም የሚያህል መንጋ ከአፋፉ ወደ ባሕር ተጣደፉና በባሕር ሰጠሙ

ፍ1 ሌጌዎን ማለት ጭፍራ ማለት ነው

14 እረኞቹም ሸሽተው በከተማውና በአገሩ አወሩነገሩም ምን እንደ ሆነ ለማየት መጡ

15 ወደ ኢየሱስም መጡአጋንንትም ያደሩበትን ሌጌዎንም የነበረበትን ሰው ተቀምጦ ለብሶም ልቡም ተመልሶ አዩና ፈሩ

16 ያዩት ሰዎችም አጋንንት ላደሩበት ሰው የሆነውንና ስለ እሪያዎቹ ተረኩላቸው

17 ከአገራቸውም እንዲሄድላቸው ይለምኑት ጀመር

18 ወደ ታንኳይቱም በገባ ጊዜ አጋንንት አድረውበት የነበረው ሰው ከእርሱ ጋር እንዲኖር ለመነው

19 ኢየሱስም አልፈቀደለትምነገር ግንወደ ቤትህ በቤተ ሰዎችህ ዘንድ ሄደህ ጌታ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገልህ እንዴትስ እንደ ማረህ አውራላቸው አለው

20 ሄዶም ኢየሱስ እንዴት ያለ ታላቅ ነገር እንዳደረገለት አሥር ከተማ በሚባል አገር ይሰብክ ጀመርሁሉም ተደነቁ

21 ኢየሱስም ደግሞ በታንኳይቱ ወደ ማዶ ከተሻገረ በኋላ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡበባሕርም አጠገብ ነበረ

22 ኢያኢሮስ የተባለ ከምኵራብ አለቆች አንዱ መጣባየውም ጊዜ በእግሩ ላይ ወደቀና

23 ታናሽቱ ልጄ ልትሞት ቀርባለችና እንድትድንና በሕይወት እንድትኖር መጥተህ እጅህን ጫንባት ብሎ አጥብቆ ለመነው

24 ከእርሱም ጋር ሄደብዙ ሕዝብም ተከተሉት አጋፉትም

25 ከአሥራ ሁለት ዓመትም ጀምሮ ደም የሚፈሳት ሴት ነበረች

26 ከብዙ ባለ መድኃኒቶችም ብዙ ተሠቃየችገንዘብዋንም ሁሉ ከስራ ባሰባት እንጂ ምንም አልተጠቀመችም

27 የኢየሱስንም ወሬ ሰምታ በስተኋላው በሰዎች መካከል መጥታ ልብሱን ዳሰሰች

28 ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ እድናለሁ ብላለችና

29 ወዲያውም የደምዋ ምንጭ ደረቀ ከሥቃይዋም እንደዳነች በሰውነትዋ አወቀች

30 ወዲያውም ኢየሱስ ከእርሱ ኃይል እንደ ወጣ በገዛ ራሱ አውቆ በሕዝቡ መካከል ዘወር ብሎልብሴን የዳሰሰ ማን ነው ? አለ

31 ደቀ መዛሙርቱምሕዝቡ ሲያጋፉህ እያየህማን ዳሰሰኝ ትላለህን ? አሉት

32 ይህንም ያደረገችውን ለማየት ዘወር ብሎ ይመለከት ነበር

33 ሴቲቱ ግን የተደረገላትን ስላወቀችእየፈራች እየተንቀጠቀጠችምመጥታ በፊቱ ተደፋች እውነቱንም ሁሉ ነገረችው

34 እርሱምልጄ ሆይእምነትሽ አድኖሻልበሰላም ሂጂ ከሥቃይሽም ተፈወሽ አላት

35 እርሱም ገና ሲናገር ከምኵራብ አለቃው ቤት ዘንድ የመጡትልጅህ ሞታለችስለ ምን መምህሩን አሁን ታደክመዋለህ ? አሉት

36 ኢየሱስ ግን የተናገሩትን ቃል አድምጦ ለምኵራቡ አለቃእመን ብቻ እንጂ አትፍራ አለው

37 ከጴጥሮስም ከያዕቆብም ከያዕቆብም ወንድም ከዮሐንስ በቀር ማንም እንዲከተለው አልፈቀደም

38 ወደ ምኵራቡ አለቃ ቤትም መጥቶ ሰዎች ሲንጫጩና ሲያለቅሱ ዋይታም ሲያበዙ አየ

39 ገብቶምስለ ምን ትንጫጫላችሁ ታለቅሳላችሁም ? ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም አላቸው

40 በጣምም ሳቁበትእርሱ ግን ሁሉን አስወጥቶ የብላቴናይቱን አባትና እናትም ከእርሱ ጋር የነበሩትንም ይዞ ብላቴናይቱ ወዳለችበት ገባ

41 የብላቴናይቱንም እጅ ይዞጣሊታ ቁሚ አላትፍችውም አንቺ ብላቴና ተነሽ እልሻለሁ ነው

42 ብላቴናይቱም የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ነበረችና ወዲያው ቆማ ተመላለሰችወዲያውም ታላቅ መገረም ተገረሙ

43 ይህንም ማንም እንዳያውቅ አጥብቆ አዞአቸውየምትበላውን ስጡአት አላቸው

6

1 ከዚያም ወጥቶ ወደ ገዛ አገሩ መጣ ደቀ መዛሙርቱም ተከተሉት

2 ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመርብዙዎችም ሰምተው ተገረሙናእነዚህን ነገሮች ይህ ከወዴት አገኛቸው ? ለዚህ የተሰጠችው ጥበብ ምንድር ናት ? በእጁም የሚደረጉ እንደነዚህ ያሉ ተአምራት ምንድር ናቸው ?

3 ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም የስምዖንም ወንድም አይደለምን ? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ አይደሉምን ? አሉይሰናከሉበትም ነበር

4 ኢየሱስምነቢይ ከገዛ አገሩና ከገዛ ዘመዶቹ ከገዛ ቤቱም በቀር ሳይከበር አይቀርም አላቸው

5 በዚያም በጥቂቶች ድውዮች ላይ እጁን ጭኖ ከመፈወስ በቀርተአምር ሊያደርግ ምንም አልቻለም

6 ስለ አለማመናቸውም ተደነቀበመንደሮችም እያስተማረ ይዞር ነበር

7 አስራ ሁለቱንም ወደ እርሱ ጠራ ሁለት ሁለቱንም ይልካቸው ጀመርበርኵሳን መናፍስትም ላይ ሥልጣን ሰጣቸው

8 ለመንገድም ከበትር በቀር እንጀራም ቢሆን ከረጢትም ቢሆን መሐለቅም በመቀነታቸው ቢሆን እንዳይዙ አዘዛቸው

9 በእግራችሁ ጫማ አድርጉ እንጂ ሁለት እጀ ጠባብ አትልበሱ አለ

10 በማናቸውም ስፍራ ወደ ቤት ብትገቡ ከዚያ እስክትወጡ ድረስ በዚያው ተቀመጡ

11 ከማይቀበሉአችሁና ከማይሰሙአችሁ ስፍራ ሁሉከዚያ ወጥታችሁ ምስክር ይሆንባቸው ዘንድ ከእግራችሁ በታች ያለውን ትቢያ አራግፉእውነት እላችኋለሁከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ በፍርድ ቀን ይቀልላቸዋል አላቸው

12 ወጥተውም ንስሐ እንዲገቡ ሰበኩብዙ አጋንንትንም አወጡ

13 ብዙ ድውዮችንም ዘይት እየቀቡ ፈወሱአቸው

14 ስሙም ተገልጦአልና ንጉሡ ሄሮድስ በሰማ ጊዜመጥምቁ ዮሐንስ ከሙታን ተነሥቶአል ስለዚህም ኃይል በእርሱ ይደረጋል አለ

15 ሌሎችምኤልያስ ነው አሉሌሎችምከነቢያት እንደ አንዱ ነቢይ ነው አሉ

16 ሄሮድስ ግን ሰምቶእኔ ራሱን ያስቈረጥሁት ዮሐንስ ይህ ነው እርሱ ከሙታን ተነሥቶአል አለ

17 ሄሮድስ የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን አግብቶ ነበርና በእርስዋ ምክንያት ራሱ ልኮ ዮሐንስን አስይዞ በወኅኒ አሳስሮት ነበር

18 ዮሐንስ ሄሮድስንየወንድምህ ሚስት ለአንተ ልትሆን አልተፈቀደም ይለው ነበርና

19 ሄሮድያዳ ግን ተቃውማው ልትገድለው ትፈልግ ነበር አልቻለችም

20 ሄሮድስ ዮሐንስ ጻድቅና ቅዱስ ሰው እንደ ሆነ አውቆ ይፈራውና ይጠባበቀው ነበርእርሱንም ሰምቶ በብዙ ነገር ያመነታ ነበር

21 በደስታም ይሰማው ነበርሄሮድስም በተወለደበት ቀን ለመኳንንቱና ለሻለቆቹ ለገሊላም ሹማምንት ግብር ባደረገ ጊዜ ምቹ ቀን ሆነላትና

22 የሄሮድያዳ ልጅ ገብታ ስትዘፍን ሄሮድስንና ከእርሱ ጋር የተቀመጡትን ደስ አሰኘቻቸውንጉሡም ብላቴናይቱንየምትወጂውን ሁሉ ለምኚኝ እሰጥሽማለሁ አላት

23 የመንግሥቴ እኩሌታ ስንኳ ቢሆን የምትለምኚውን ሁሉ እሰጥሻለሁ ብሎ ማለላት

24 ወጥታም ለእናትዋምን ልለምነው ? አለችእርስዋምየመጥምቁን የዮሐንስን ራስ አለች

25 ወዲያውም ፈጥና ወደ ንጉሡ ገብታየመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በወጭት አሁን ልትሰጠኝ እወዳለሁ ብላ ለመነችው

26 ንጉሡም እጅግ አዝኖ ስለ መሐላው ከእርሱም ጋር ስለ ተቀመጡት ሊነሣት አልወደደም

27 ወዲያውም ንጉሡ ባለ ወግ ልኮ ራሱን እንዲያመጣ አዘዘውሄዶም በወኅኒ ራሱን ቈረጠ

28 ራሱንም በወጭት አምጥቶ ለብላቴናይቱ ሰጣትብላቴናይቱም ለእናትዋ ሰጠች

29 ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው መጡ በድኑንም ወስደው ቀበሩት

30 ሐዋርያትም ወደ ኢየሱስ ተሰብስበው ያደረጉትንና ያስተማሩትን ሁሉ ነገሩት

31 እናንት ራሳችሁ ብቻችሁን ወደ ምድረ በዳ ኑና ጥቂት ዕረፉ አላቸውየሚመጡና የሚሄዱ ብዙዎች ነበሩናለመብላት እንኳ ጊዜ አጡ

32 በታንኳውም ብቻቸውን ወደ ምድረ በዳ ሄዱ

33 ሰዎችም ሲሄዱ አዩአቸው ብዙዎችም አወቁአቸውና ከከተሞች ሁሉ በእግር እየሮጡ ወዲያ ቀደሙአቸው ወደ እርሱም ተሰበሰቡ

34 ኢየሱስም ወጥቶ ብዙ ሕዝብ አየና እረኛ እንደሌላቸው በጎች ስለ ነበሩ አዘነላቸውብዙም ነገር ያስተምራቸው ጀመር

35 በዚያን ጊዜም ብዙ ሰዓት ካለፈ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀርበውቦታው ምድረ በዳ ነው አሁንም መሽቶአል

36 የሚበሉት የላቸውምና በዙሪያ ወዳሉ ገጠሮችና መንደሮች ሄደው እንጀራ ለራሳቸው እንዲገዙ አሰናብታቸው አሉት

37 እርሱ ግን መልሶእናንተ የሚበሉትን ስጡአቸው አላቸውሄደን እንጀራ በሁለት መቶ ዲናር እንግዛላቸውን ? እንዲበሉም እንስጣቸውን ? አሉት

38 እርሱምስንት እንጀራ አላችሁ ? ሂዱና እዩ አላቸውባወቁም ጊዜአምስትሁለትም ዓሣ አሉት

39 ሁሉንም በየክፍሉ በለመለመ ሣር ላይ እንዲያስቀምጡአቸው አዘዛቸው

40 መቶ መቶውና አምሳ አምሳው እየሆኑ በተራ በተራ ተቀመጡ

41 አምስቱንም እንጀራ ሁለቱንም ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ አሻቅቦ አየና ባረከእንጀራውንም ቈርሶ እንዲያቀርቡላቸው ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ

42 ሁለቱን ዓሣ ደግሞ ለሁሉ ከፈለሁሉም በልተው ጠገቡ

43 ከቍርስራሹም አሥራ ሁለት መሶብ የሞላ አነሡ ከዓሣውም ደግሞ

44 እንጀራውንም የበሉት ወንዶቹ አምስት ሺህ ነበሩ

45 ወዲያውም ሕዝቡን ሲያሰናብት ሳለ ደቀ መዛሙርቱ በታንኳ ገብተው ወደ ማዶ ወደ ቤተ ሳይዳ እንዲቀድሙት ግድ አላቸው

46 ካሰናበታቸውም በኋላ ሊጸልይ ወደ ተራራ ወጣ

47 በመሸም ጊዜ ታንኳይቱ በባሕር መካከል ሳለች እርሱ ብቻውን በምድር ላይ ነበረ

48 ነፋስ ወደ ፊታቸው ነበረና እየቀዘፉ ሲጨነቁ አይቶከሌሊቱ በአራተኛው ክፍል በባሕር ላይ እየሄደ ወደ እነርሱ መጣሊያልፋቸውም ይወድ ነበር

49 እነርሱ ግን በባሕር ላይ ሲሄድ ባዩት ጊዜ ምትሀት መሰላቸውና ጮኹ

50 ሁሉ አይተውታልናታወኩምወዲያውም ተናገራቸውናአይዞአችሁእኔ ነኝአትፍሩ አላቸው

51 ወደ እነርሱም ወደ ታንኳይቱ ገባነፋሱም ተወበራሳቸውም ያለ መጠን እጅግ ተገረሙ

52 ስለ እንጀራው አላስተዋሉምናነገር ግን ልባቸው ደንዝዞ ነበር

53 ተሻግረውም ወደ ምድር ወደ ጌንሴሬጥ ደረሱ ታንኳይቱንም አስጠጉ

54 ከታንኳይቱም ሲወጡ ወዲያው አውቀውት

55 በዚያች አገር ሁሉ ዙሪያ ሮጡና እርሱ እንዳለ ወደ ሰሙበት ስፍራ ሕመምተኞችን በአልጋ ላይ ያመጡ ጀመር

56 በገባበትም ስፍራ ሁሉመንደርም ከተማም ገጠርም ቢሆንበገበያ ድውዮችን ያኖሩ ነበርየልብሱንም ጫፍ እንኳ ሊዳስሱ ይለምኑት ነበር የዳሰሱትም ሁሉ ዳኑ

7

1 ፈሪሳውያንና ከጻፎች ወገን ከኢየሩሳሌም የመጡትም ወደ